ሜልበርን ላይ ተጥሎ ያለው የኮሮናቫይረስ ገደብ ከጥቂት ለውጥ ጋር ከዛሬ እኩለ ለሊት ጀምሮ ያበቃል

*** ከቤት ውጪ የፊት ጭምብል ማጥለቅ ግድ ይላል

face mask

A man is seen wearing a face mask as a preventative measure against coronavirus in Melbourne, Australia. Source: Getty

ምንም እንኳ በዛሬው ዕለት ቪክቶሪያ አራት በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎችን ብታስመዘግብም፤ ሜልበርንና ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ ተጥለው ያሉ የኮረናቫይረስ ገደቦች በተያዘላቸው ዕቅድ ይነሳሉ።

የቪቶሪያ ተጠባባቂ ፕሪሚየር ጄም ሜሊኖ ገደቦቹ ከዛሬ ሐሙስ ጁን 10 ከምሽቱ 11:59pm ጀምሮ ግብር ላይ መዋላቸው እንደሚያበቃ አስታውቀዋል።

ይሁንና በትናንትናው ዕለት ገደቡ ሲነሳ ከቤት ውጪ የፊት ጭምብል ማጥለቅ ግድ እንደማይል ቢነገርም ከዛሬው የቫይረስ ክስተት ጋር ተያይዞ ነዋሪዎች ከቤት ውጪ የፊት ጭምብል ማጥለቅ አለባቸው በሚለው ማስተካከያ ተደርጎበታል።

በአሁኑ ወቅት ቪክቶሪያ ውስጥ 78 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተው ያሉ ሲሆን፤ በትናንትናው ዕለት 23,679 የቪክቶሪያ ነዋሪዎች የቫይረስ ምርመራ አካሂደዋል 20,784 ክትባት ተከትበዋል። 


Share
Published 10 June 2021 3:05pm
By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends