ትዕግስት አሰፋ የፓሪስ ኦሎምፒክ የብር ሜዳል ባለቤት ሆነች

ኢትዮጵያ ከ184 ተወዳዳሪ ሀገራት ወደ 45ኛ ደረጃ ከፍ ብላለች።

Tigist Assefa.jpg

Paris, France - 11 August 2024; Tigst Assefa of Team Ethiopia celebrates finishing second place after the women's marathon at Esplanade des Invalides during the 2024 Paris Summer Olympic Games in Paris, France. Credit: Sam Barnes/Sportsfile via Getty Images

እሑድ ነሐሴ 5 / ኦገስት 11 በፓሪስ ኦሎምፒክ የፍፃሜ ዋዜማ በተካሔደ የሴቶች ማራቶን ትዕግስት አሰፋ 2 ሰዓት ከ22 ደቂቃ 58 ሰከንድ በመጨረስ የሁለተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቅቃለች።

ኔዘርላንድስን ወክላ የሮጠችው የኢትዮጵያ ተወላጇ ሲፋን ሐሰን 2 ሰዓት ከ22 ደቂቃ 55 ሰከንድ በሆነ ውጤት በማሸነፍ የወርቅ ሜዳል ባለቤት ሆናለች።

በእዚሁ በፓሪስ ኦሎምፒክ የ5000 እና 10 ሺህ ሜትሮች የወርቅ ሜዳል አሸናፊ በመሆን በልዩ የኦሎምፒክ ታሪክ የክብር ሥፍራ ይዛለች።

ኬንያዊቷ ሄለን ኦቢሪ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ10 ሰከንድ በሆነ ውጤት 3ኛ ሆና ለነሐስ ሜዳል በቅታለች።

ኢትዮጵያ ትዕግስት አሰፋን ጨምሮ በአራት የኦሎምፒክ ውድድሮች በሴት አትሌቶቿ 2 የወርቅ 1 የብር እና 1 የነሐስ ሜዳሎችን አግኝታለች።

  • ፋጡማ ሮባ፤ በ1996 የአትላንታ ኦሎምፒክ ወርቅ
  • ቲኪ ገላና፤ በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ ወርቅ (የኦሎምፒክ ሬኮርድ በመስበር 2:23:07)
  • ማሬ ዲባባ፤ በ2016 የሪዮ ዴ ጄኒሮ ኦሎምፒክ ነሐስ
  • ትዕግስት አሰፋ፤ በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ የብር ሜዳሎችን አግኝታለች።
በፓሪስ ኦሎምፒክ 16ኛ የውድድር ዕለት ድረስ በ32 የስፖርት ዘርፎች በተካሔዱ ውድድሮች ቻይናና ዩናይትድ ስቴትስ የሜዳል ሠንጠረዥ ላይ አንደኛና ሁለተኛ በመሆን እየተፈራረቁ ደረጃዎቻቸውን ይዘው አሉ፤


  • ቻይና፤ 39 ወርቅ 27 ብር 24 ነሐስ በድምሩ 90 ሜዳሎችን በማግኘት 1ኛ
  • ዩናይትድ ስቴትስ፤ 38 ወርቅ 42 ብር 42 ነሐስ በድምሩ 122 ሜዳሎችን በማግኘት 2ኛ
  • አውስትራሊያ፤ 18 ወርቅ 18 ብር 14 ነሐስ በድምሩ 50 ሜዳሎችን በማግኘት 3ኛ
  • ኢትዮጵያ 1 ወርቅ 3 ብር በድምሩ 4 ሜዳሎችን በማግኘት 45ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends