ጨፌ ኦሮሚያ የአቶ ታየ ደንደአን ያለመከሰስ መብት አነሳ

የአቶ ታየ ደንደአ በምክር ቤት አባልነት ያለመከሰስ መብት የተገፈፈው ጨፌ ኦሮሚያ ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤውን ባካሔደበት ወቅት ነው።

Taye D.png

Former state minister for peace, Taye Dendea. Credit: ENA

የጨፌ ኦሮሚያ ጉባኤ ከውሳኔ ላይ የደረሰው የካቲት 11 ለስድስተኛ ዓመት ሶስተኛ የሥራ ዘምን በተሰየመበት ዕለት ነው።

የአቶ ታየ ያለመከሰስ መብት የተገፈፈውም በ439 የድጋፍና 14 ድምፀ ተአቅቦ ውጤት መሠረት ነው።

የቀድሞው የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ታየ ደንደአ በተጠርጣሪነት በእሥር ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ለእሥራት የተዳረጉትም በፌዴራል የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ነው።

ግብረ ኃይሉ ታህሳስ 2 ቀን 2016 ባወጣው መግለጫ አቶ ታየ "ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በተሳሰር ለጥፋት ተልዕኮ በሕቡዕ ሲሰራ ተደርሶበታል" ብሏል።

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends