የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዎንግ ቻይና የገቡት በቤጂንግ ሰዓት አቆጣጠር ማክሰኞ 10.38pm በአውስትራሊያ ሰዓት አቆጣጠር ረቡዕ 1.38am AEDT ነው።
ሚኒስትር ዎንግ ቤጂንግ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሱ በቻይና የአውስትራሊያ አምባሳደር ግራሃም ፍሌቸር አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ከቻይናው አቻቸው ዋንግ ዪ ጋር ተገናኝተው ሲነጋገሩ፤ ቻይና በዓመት ከ200 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ በሚያስገኙ በተለያዩ የአውስትራሊያ ምርቶች ላይ የጣለችቻቸው ማዕቀቦች ዋነኛ የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሚሆን ይጠበቃል።
በታካይነትም አውስትራሊያዊቷን ጋዜጠኛ ቼንግ ሊይን ጨምሮ ቻይና ውስጥ በእሥር ላይ የሚገኙ አውስትራሊያውያን ጉዳይም እንደሚነሳ ይታመናል።
ሴናተር ዎንግ ቻይና እንደገቡ ከቤጂንግ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከረጅም ዓመታት በኋላ ቻይና መገኘታቸው ማለፊያ እንደሆነ ጠቅሰው" የሁለቱን አገራት 50ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማክበር እንዲያስችል እዚህ በመገኘቴ ለቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ዕውቅናና ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል።
አያይዘውም፤ የጉብኝታቸው አንዱ ስኬት ንግግሩ እራሱ መሆኑን ልብ አሰኝተው፤ በርካታ ዕልባት ሊበጅላቸው የሚሹ ጉዳዮም እንዳሉ አመላክተዋል።