የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ ከቻይናው አቻቸው ዋንግ ዪ ጋር ቤጂንግ ላይ የተገናኙት ረቡዕ ምሽት ሲሆን፤ ይህም ከአራት ዓመታት ወዲህ የመጀመሪያው የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጉብኝት ነው።
የሚኒስትሯ ጉዞ በቻይና አውስትራሊያ ላይ ተጥለው ያሉት ማዕቀቦች እንዲነሱና ቻይና ውስጥ በእሥር ላይ የሚገኙ ሁለት አውስትራሊያውያን ዜጎች እንዲለቀቁ ለማስቻል በር ከፋች ይሆናል የሚሉ ተስፋዎችን አሳድሯል።
ሴናተር ዎንግ በቤጂንግ ለ50ኛው የአውስትራሊያና ቻይና ዲፖማሲያዊ ግንኙነት በዓል በአካል መገኘታቸው ያስደሰታቸው መሆኑን ገልጠው፤
"በዚህች ታሪካዊ ቀን ይህ ግንኙነት እዚህ እንዲደርስ አያሌዎች አስተዋፅዖዎቻቸውን አበርክተዋል" በማለት ቀደም ሲል ከምሥረታው እስከ ዘለቄታው ልዩ ሚና ለተጫወቱ አውስትራሊያውያንና ቻይናውያን ዕውቅናን ቸረዋል።

Australian Foreign Minister Penny Wong during a meeting with Chinese Foreign Minister Wang Yi at Diaoyutai State Guesthouse in Beijing, China, Wednesday, December 21, 2022. Credit: AAP Image/Lukas Coch
"ከቻይና ጋር ያለንን ግንኙነት ማርጋት የአውስትራሊያ ጥቅም እንደሁ የምናምን መሆኑን መንግሥት ግልፅ አድርጓል። እንዲሁም የግንኙነቱ መርጋት ለቻይናም ጥቅም ጭምር መሆኑንም እንደምናምን ግልፅ አድርገናል። በአውስትራሊያና ቻይናና መካከል ሁሉን አካታች ስትራቴጂያዊ ወዳጅነት ለሁለቱ አገራት ትሩፋትን የሚያስገኝ የንግግርና ተሳትፎ ሥነ ጥበብ ነው ስንል አተያያችንን በመግለፁ እንቀጥላለን። ልዩነቶቻችንን በብልሃት መፍታት ከቻልን፤ የሁለትዮሽ ግኑኙነታችንን ማጎልበትና የጋራ ጥቅሞቻችንን ማስከበር ይቻለናል ስንል አተያያችንን በመግለፁ እንቀጥላለን። ይህ ትውልድ በብልሃት እንዲፈታው ገጥሞት ያለው ተግዳሮትም ይህ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

Australian Foreign Minister Penny Wong and Chinese Foreign Minister Wang Yi unveil a commemorative envelope during a ceremony on the 50th anniversary of the establishment of diplomatic relations between Australia and China, at Diaoyutai State Guesthouse in Beijing, China, Wednesday, December 21, 2022. Credit: AAP Image/Lukas Coch