የኒው ሳውዝ ዌይልስ ሌበር ፓርቲ ራሱን ችሎ አብላጫ ወንበር ያለው መንግሥት ለማቆም የሚያስችሉትን 47 የምክር ቤት ወንበሮች በእርግጥኝነት እንደሚያገኝ የተጠቆመ ሲሆን፤ ከቶውንም የድምፅ ቆጠራው ሲያበቃ እስከ 50 የምክር ቤት ወንበሮችን ሊያሸንፍ እንደሚችል በABC የምርጫ ተንታኝ ተገምቷል።
በሌላ በኩል የቀድሞው የሊብራል ፓርቲ መሪና የኒው ሳውዝ ዌይልስ ፕሪሚየር ዶሜኒክ ፔሮቴይ ፓርቲያቸው በምርጫው ድል ለመነሳቱ ሙሉ ኃላፊነትን እንደሚወስዱ ገልጠው፤ ያም በመሆኑ በፈቃዳቸው ከሊብራል ፓርቲ መሪነት ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታውቀዋል።

NSW Premier Dominic Perrottet with his wife Helen Perrottet and daughter Celeste arrive to cast their votes on NSW state election day. Credit: AAP / AAP
ሲመለከቱት የነበረውን የእግር ኳስ ጨዋታ አቋርጠው የሌበር የድል ብስራት መታደሚያ በሆነው አዳራሽ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ
"የኒው ሳውዝ ዌይልስ ሕዝብ በጋራ ሆኖ የተሻለ መፃኢ ጊዜን መርጧል። በዛሬዋ ምሽት የኒው ሳውዝ ዌይልስ አዲስ ጅማሮ ይጀመራል... የሚጀምረውም በታላቅ መሪ ነው" ብለዋል።

NSW Labor Leader Chris Minns is congratulated by Prime Minister Anthony Albanese after the state election result. Source: AAP / DEAN LEWINS/AAPIMAGE
የሌበር ፓርቲ ቀደም ሲል ከሁለኛው ጦርነት በኋላ ከተቃዋሚነት ተነስቶ ለመንግሥትነት የበቃው በ1976 በኔቪል ራን እና በ1995 በቦብ ካር መሪነት ነው።