የኒጄር ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ደጋፊዎች የገዢውን ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት አጋዩ

የአውስትራሊያ በናይጄሪያ 3 ለ 2 መሸነፍ የማቲልዳስን ለጥሎ ማለፍ ግጥሚያ መድረስ ጥርጣሬ ውስጥ ጥሏል

Niger Tensions

Supporters of mutinous soldiers demonstrate in the capital of Niger, Niamey. Source: AP / AAP

የኒጄር ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ደጋፊዎች በመዲናይቱ ኒአሜይ የሚገኘውን የገዢው ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት በእሳት አጋይተዋል።

የኒጄር ፕሬዚደንት መሐመድ ባዙም እስካሁን በመፈንቅለ መንግሥት ፈፃሚዎቹ እግት ስር ያሉ ሲሆን፤ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስና የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ፕሬዚደንቱ ከእገታ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።
የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ካሪን ዤን-ፒየር ኒጄር ዩናይትድ ስቴትስ ሁኔታውን ኒጄር በሚገኘው ኤምባሲዋ በኩል እየተከታተለች እንደሁ ጠቅሰው እዚያ የሚገኙ አሜሪካውያን ከፍ ያለ ጥንቃቄን እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

አያይዘውም "እኛ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለተመረጠ ፕሬዚደንት ጠንካር ድጋፍ እሰጣለን፤ በመሆኑም ስልጣንን በኃይል ለመያዝ የሚደረግ ማናቸውንም ዓይነት ጥረት በብርቱ እናወግዛለን" ብለዋል።

የሴቶች እግር ኳስ የዓለም ዋንጫ

ትናንት ሐሙስ ምሽት በአውስትራሊያ ማቲልዳስና በናይጄሪያ ሱፐር ፋልከንስ ብሔራዊ የሴቶች እግር ኳስ ቡድናት መካከል በተካሔደው ግጥሚያ የማቲልዳስ በሱፐር ፋልከንስ 3 ለ 2 መረታት፤ የዋንጫ ባለቤት ይሆናሉ ተብለው ትልቅ ተስፋ በተጣለባቸው የማቲልዳስ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች ላይ ብርቱ ተፅዕኖ አሳድሯል።
Nigeria players.jpg
Nigeria players pose for a group photo before the Australia and New Zealand 2023 Women's World Cup Group B football match between Australia and Nigeria at Brisbane Stadium in Brisbane on July 27, 2023. Credit: PATRICK HAMILTON/AFP via Getty Images
አውስትራሊያ ሰኞ ሐምሌ 24 / ጁላይ 31 የመጨረሻ የምድብ ማጠናቀቂያ ግጥሚያዋን ከካናዳ ታደርጋለች።
Matildas.jpg
The Matildas must beat Canada on Monday to progress to the Women's World Cup knockout round. Credit: AAP / Darren England
አውስትራሊያ ለቀጣዩ የጥሎ ማለፍ ውድድር ከምድቧ አላፊ ከሚሆኑት ሁለት ቡድናት ውስጥ አንዷ ሆና ለማለፍ ግጥሚያውን የግድ በአሸናፊት መፈፀም ይጠበቅባታል።

FIFA.jpg
Credit: FIFA

Share
Published 28 July 2023 3:23pm
Updated 28 July 2023 3:29pm
By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends