የኒጄር ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ደጋፊዎች በመዲናይቱ ኒአሜይ የሚገኘውን የገዢው ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት በእሳት አጋይተዋል።
የኒጄር ፕሬዚደንት መሐመድ ባዙም እስካሁን በመፈንቅለ መንግሥት ፈፃሚዎቹ እግት ስር ያሉ ሲሆን፤ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስና የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ፕሬዚደንቱ ከእገታ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።
የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ካሪን ዤን-ፒየር ኒጄር ዩናይትድ ስቴትስ ሁኔታውን ኒጄር በሚገኘው ኤምባሲዋ በኩል እየተከታተለች እንደሁ ጠቅሰው እዚያ የሚገኙ አሜሪካውያን ከፍ ያለ ጥንቃቄን እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
አያይዘውም "እኛ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለተመረጠ ፕሬዚደንት ጠንካር ድጋፍ እሰጣለን፤ በመሆኑም ስልጣንን በኃይል ለመያዝ የሚደረግ ማናቸውንም ዓይነት ጥረት በብርቱ እናወግዛለን" ብለዋል።
የሴቶች እግር ኳስ የዓለም ዋንጫ
ትናንት ሐሙስ ምሽት በአውስትራሊያ ማቲልዳስና በናይጄሪያ ሱፐር ፋልከንስ ብሔራዊ የሴቶች እግር ኳስ ቡድናት መካከል በተካሔደው ግጥሚያ የማቲልዳስ በሱፐር ፋልከንስ 3 ለ 2 መረታት፤ የዋንጫ ባለቤት ይሆናሉ ተብለው ትልቅ ተስፋ በተጣለባቸው የማቲልዳስ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች ላይ ብርቱ ተፅዕኖ አሳድሯል።

Nigeria players pose for a group photo before the Australia and New Zealand 2023 Women's World Cup Group B football match between Australia and Nigeria at Brisbane Stadium in Brisbane on July 27, 2023. Credit: PATRICK HAMILTON/AFP via Getty Images

The Matildas must beat Canada on Monday to progress to the Women's World Cup knockout round. Credit: AAP / Darren England

Credit: FIFA