የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በተሰየሙ የሰላም ልዑካን ቡድን እየተመራ ያለው የኢትዮጵያ መንግሥትና የሕወሓት ተደራዳሪዎች መካከል ቀጥሎ ያለው ቋሚ ከግጭት ዕቀባ ስምምነት ሂደት ትግበራ ክትትል ስብሰባ ዳግም ዲሴምበር 22/ ታሕሳስ 23 ናይሮቢ ከተማ ተካሂዷል።
ስብሰባው የጋራ ቁጥጥር፣ ማጣራትና አከባበር ዘዴ ውል ማጣቀሻ ላይ ተወያይቶ ከማጠቃለያ ደርሷል። እንዲሁም፤ የትጥቅ ፍቺ፣ ብተናና ዳግም ቅልቅል ላይም ተነጋግሯል።
የገዲብ አዛዦቹ ስብሰባ የተካሔደው በአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚደንት በሚመራው ልዑክ ቡድን ሲሆን፤ በዕለቱም የልዑካን ቡድን አባላቱ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዚደንት ዶ/ር ፉምዚሌ ምላምቦ ጉካ አማካይነት ነው።