የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ አውስትራሊያ የመጀመሪያ ዙር ክትባት 90 ፐርሰንት ዒላማዋን አለፈች

*** ቪክቶሪያ ውስጥ 1,115 በቫይረስ ሲጠቁ፤ ዘጠኝ ሕይወታቸውን አጥተዋል።

COVID-19 update

Higher vaccination rate in the country would mean greater freedoms. Source: AAP

  • የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያን ቁጥር 90 ፐርሰንት አለፈ።
  • ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የፌዴራል መንግሥቱ በቪክቶሪያ ወረርሽኝ ድንጋጌዎች ጣልቃ እንደማይገባ አስታወቁ። 
  • የኩዊንስላንድ ፕሪሚየር አናስታዥያ ፓለሼይ የ12 ክፍል መልቀቂያ የጨረሱ ተማሪዎችን ዓመታዊ ፓርቲ እንደማይሰርዙ ገልጠው፤ ሆኖም ምንጩ ያልታወቀ ቫይረስ ከተከሰተ ግና ብርቱ ውሳኔ ለማሳለፍ እንደማያመነቱ አሳሰቡ።
  • ታዝማኒያ ዕድሜያቸው ከ 16-24 ያሉና ክትባት የተከተቡ በቡድን የመሰብሰብና የዳንስ ፌስቲቫሎች ላይ ሙሉ ክትባት የተከተቡ ሰዎችን አስመልክቶ የገደቦች ክለሳ እያደረገች ነው።
  • የምዕራብ አውስትራሊያ ክትባት ኮሚሽነር ክሪስ ዳውሰን የክትባት ደረጃው ዝቅተኛ የሆነባቸው ነባር ዜጎች መኖሪያ ሥፍራ ላሉ የማኅበረሰብ አረጋውያን በግል ተማፅኖ አቀረቡ። 
  • ከኖቬምበር 15 ጀምሮ ሲድኒ ውስጥ በብርቱ አስፈላጊ ያልሆኑ የቀዶ ሕክምና ግልጋሎቶች በሙሉ አቅም ይሰጣል። 

ኮቪድ-19 ስታቲስቲክስ፤

ቪክቶሪያ ውስጥ 1,115 በቫይረስ ሲጠቁ፤ ዘጠኝ ሕይወታቸውን አጥተዋል።  
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 286 ነዋሪዎቿ በቫይረስ መጠቃታቸውንና የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስታወቀች። 
ኩዊንስላንድ ውስት ሁለት ሰዎች በቫይረስ ሲያዙ፤ የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ 15 ነዋሪዎች ተጠቅተዋል። 

የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤

ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ  ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።





በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤

የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤


 
 

የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤

 
 
 


Share
Published 12 November 2021 6:29pm
Updated 12 November 2021 6:32pm
By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends