የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ አውስትራሊያ ሙሉ ክትባት ለተከተቡ መንገደኞች ከዲሴምበር 1 ጀምሮ በሯን ክፍት ልታደርግ ነው

*** ቪክቶሪያ ውስጥ 1,029 በቫይረስ ሲጠቁ፤ ሶስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

COVID-19 update

Passengers arrive at Melbourne International Airport. Source: AAP

ከዲሲምበር 1 ጀምሮ ሙሉ ክትባት የተከተቡና መመዘኛን ያሟሉ ባለ ቪዛዎች የልዩ ፈቃድ ማመልከቻ ሳያስገቡ ወደ አውስትራሊያ መዝለቅ ይችላሉ። 

መመዘኛን ያሟሉ ባለ ቪዛዎች ባለ ሙያ ሠራተኞችና ዓለም አቀፍ ተማሪዎች፣ የሽርሽርና ጊዜያዊ ሠራተኞች፣ የሰብዓዊ ቪዛና ጊዜያዊ ቪዛ ያላቸው ስደተኞችን ያካትታል። ወደ አውስትራሊያ ከመዝለቃቸው በፊትም  ሙሉ ክትባት መከተብ ይኖርባቸዋል፣ ከትባት የተከተቡበትን ማስረጃ ሊያቀርቡ ይገባል፣ ጉዞ ከመጀመራቸው ሶስት ቀናት ቀደም ብለው ከቫይረስ ነፃ መሆናቸውን የሚያመለክት የPCR ምርመራ ውጤት ሊኖራቸው ግድ ይላል።

በተጨማሪም ከዲሴምበር 1 ጀምሮ አውስትራሊያ በጃፓንና ኮሪያ ያሉ ዜጎችን ልዩ ፈቃድ ሳያሻቸው ትቀበላለች።

ኮቪድ-19 ስታቲስቲክስ፤

ቪክቶሪያ ውስጥ 1,029 በቫይረስ ሲጠቁ፤ ሶስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።  

ኒው ሳውዝ ዌይልስ 180 ነዋሪዎቿ በቫይረስ መጠቃታቸውንና የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉን አስታወቀች። 

ኖርዘን ቴሪቶሪ ውስጥ ሁለት ሰዎች በቫይረስ ተይዘዋል። ካትሪን ላይ ተጥሎ ያለው ገደብ እስከ ኖቬምበር 24 ከምሽቱ 6pm ድረስ ተራዝሟል።

በቫይረስ ተይዘዋል።

 


ወሸባና ገደቦች ክፍለ አገር በክፍለ አገር፤

ጉዞ

 የኮቪድ-19 እና የጉዞ መረጃ 

የገንዘብ እርዳታ

ሙሉ ክትባት የተከተቡ ነዋሪዎች ቁጥር 70 እና 80 ፐርሰንት በደረሰባቸው ክፍለ ኣገራት የኮቪድ-19 Disaster Payment ይለወጣል፤  


 

 


Share
Published 22 November 2021 4:27pm
By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends