- የኒው ሳውዝ ዌይልስ ዳቦ ሪጅን ገደብ ተጣለበት
- ቪክቶሪያ ውስጥ አምስት የቫይረስ ምንጮች ምርመራ እየተደረገባቸው ነው
- ኬይንስ ላይ የተጣለው ገደብ ተነሳ
ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 20 ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል። አምስቱ ቀደም ሲል ወረርሽኙ ተዛምቶባቸው ከነበሩ ሥፍራዎች አይደሉም። ስድስቱ የማኅበረሰብ ተጋቦት ናቸው።
እንደራሴ ዳንኤል አንድሩስ ሜልበርን ላይ ተጥሎ ያለው ገደብ እስከ ሐሙስ ኦገስት 19 መራዘሙን አስታወቁ።
ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ በዛሬው ዕለት 344 ሰዎች በቫይረስ የተያዙባት ሲሆን 65 ያህሉ የማኅበረሰብ ተጋቦት ናቸው። አንድ ዕድሜያቸው በ90ዎቹ ያሉና አንድ በ30ዎቹ ዕድሜ ውስጥ ያለ ግለሰብ በኮቪድ-19 ተጠቅተው ሕይወታቸው አልፏል። ሁለቱም ክትባት ያልተከተቡ ነበሩ።
የኒው ሳውዝ ዌይልስ ዳቦ ሪጂን ላይ ከዛሬ ረቡዕ ኦገስት 11 ከቀትር በኋላ 1pm ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ገደብ ተጥሏል። ለገደቡ መጣል አስባብ የሆነውም ሁለት ግለሰቦች በቫይረስ ተጠቅተው በመገኘታቸው ነው።
ዋና የጤና ኃላፊ ዶ/ር ኬሪ ቻንት እንደገለጡት በፅኑዕ ህሙማን ክፍል በመታከም ካሉት 62 ሰዎች ውስጥ 57ቱ ያልተከተቡ ሲሆን አምስቱ የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ ናቸው።
ኩዊንስላንድ
ኩዊንስላንድ ውስጥ አራት ሰዎች በቫይረስ የተጠቁ ሲሆን ሁሉም ቀደም ሲል ቫይረሱ ተዛምቶባቸው ያሉ ሥፍራዎች ነዋሪዎችና ወሸባ ገብተው የሚገኙ ናቸው።
ኬይንስ እና ያራባህ ላይ ተጥለው የነበሩት ገደቦች ከዛሬ 4 pm ጀምሮ ይረግባሉ፤ የተወሰኑ ገደቦች ጸንተው ይቀጥላሉ .
ዋና የጤና ኃላፊ ዶ/ር ጃኔት ያንግ ስር የሰደደ ሕመም ያለባቸውና ዕድሜያቸው ከ12-15 ያሉ ልጆች ለክትባት እንዲመዘገቡ አሳስበዋል።
ወሸባ፣ ጉዞ፣ የክሊኒክ ምርመራና የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ
የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤
ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።
- ዜናዎችና መረጃዎችን ከ 60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች በመጎብኘት ይመልከቱ።
- ስለ ሚኖሩበት ክፍለ አገር ጠቃሚ መረጃዎችን ከፈለጉ፤ , , , , , , ይጫኑ።
- መረጃዎችን በቋንቋዎ ለማግኘት ይህን ይጫኑ .
በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤
የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤
የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤