የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ ኳንታስ ዓለም አቀፍ በረራ ሊጀምር ነው

*** ከኖቬምበር 1 ጀምሮ ሙሉ ክትባት ተከትበው ከባሕር ማዶ ወደ ቪክቶሪያ የሚመጡ አውስትራሊያውያን ወሸባ እንዳይገቡ ተወሰነ።

COVID-19 update

Melbourne has emerged from the world's longest lockdown, and as vaccination rates continue to rise. Source: AAP

  • የቪክቶሪያ ገደብ በላላበት ዕለት 16 ሰዎች በኮቪድ-19 ሕይወታቸው አለፈ፤  2,189 በቫይረስ ተጠቁ።
  • ኳንታስ የዓለም አቀፍ በረራ ዕቅዱን አሻሻለ
  • ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን መንግሥት ከሲንጋፖር ጋር የመንገድኞች በረራ ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረቡን ጠቆሙ

 ቪክቶሪያ

ቪክቶሪያ ውስጥ 2,189 በኮቪድ-19 ተጠቁ፤ 16 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። ሜልበርን በዓለም ረጅም ከተባለው የኮሮናቫይረስ ገደብ ቆይታ ተላቅቃለች።

ሙሉ ክትባት የተከተቡ የከፍለ አገሪቱ ነዋሪዎች ቁጥር ቀደም ብሎ ታስቦ ከነበረው ኖቬምበር 5 በአንድ ሳምንት ቀደም ብሎ ኦክቶበር 30 ላይ 80 ፐርሰንት ይደርሳል ተብሎ ተገምቷል። 

እንደራሴ ዳንኤል አንድሩስ ከኖቬምበር 1 ጀምሮ ሙሉ ክትባት ተከትበው ከባሕር ማዶ ወደ ቪክቶሪያ የሚመጡ አውስትራሊያውያን ወሸባ እንዳይገቡ መወሰኑን አስታወቀዋል።  

አቅራቢያዎ የሚገኝ የክትባት ማዕከልን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ   

ኒው ሳውዝ ዌይልስ
 ኒው ሳውዝ ዌይልስ 345 ነዋሪዎቿ በቫይረስ ተጠቁ። አምስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። 

ኳንታስ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ሠራተኞቹን ወደ ሥራ መልሶ የዓለም አቀፍ በረራውን ለመጨመር ማቀዱን ባስታወቀበት በዛሬው ዕለት፤ ሲድኒ አውሮፕላን ማረፊያ የተገኙት እንደራሴ ዶሚኒክ ፔሮቴይ ኒው ሳውዝ ዌይልስ "የመልሶ መቋቋም ማኮብኮቢያ" ላይ እንደምትገኝ ተናግረዋል። 

በሥፍራው ተገኝተው የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰንም በበኩላቸው አውስትራሊያውያን ወደ ሲንጋፖር መጓዝ እንዲችሉ በመጪው ሳምንት ከስምምነት ላይ ለመድረስ የመቋጫ ንግግር ላይ መኮኑን አመላክተዋል።  

አቅራቢያዎ የሚገኝ የክትባት ማዕከልን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ   

የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ

የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ውስጥ 13 ሰዎች በቫይረስ የተጠቁ ሲሆን ዕድሜያቸው 12 እና ከዚያ በላይ የሆነ 84 ፐርሰንት ነዋሪዎች ሙሉ ክትባት ተከትበዋል። 

የክትባት ቀነ ቀጠሮ ለማስያዝ አሁኑኑ ይህን ይጫኑ  

ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ

  • ኩዊንስላንድ ውስጥ አንድም በቫይረስ የተጠቃ ሰው አልተመዘገበም፤ ይሁንና የሎጋን ከትባት መጠን አሳሳቢ ሆኗል። በነገው ዕለት በ100 የትምህርት ቤት ቅጥር ግቢዎች ውስጥ መጠነ ሰፊ 'የልዕለ ቅዳሜ' ክትባት ይካሄዳል።
የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤

ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ  ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።





በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤

የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤


 
 

የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤

 
 
 

 

 

 


Share
Published 22 October 2021 7:45pm
By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends