- ሰሜን ቴሪቶሪ ውስጥ የመጀመሪያ የኮቪድ ሞት ተመዘገበ። እስካሁን ድረስ አውስትራሊያ ውስጥ ከኮቪድ ጋር በተያያዘ ሞት ስታስመዘግብ የቆየችው ኖርዘን ቴሪቶሪ ብቻ ነበረች።
- የፌዴራል ጤና ሚኒስትር የብሔራዊ ፍኖተ ካርታ ላይ ለውጥ እንደማይደረግ አስታወቀ።
- የአፍሪካውያን-አውስትራሊያ ማኅበረሰብ መሪዎች መንግሥት የኦሚኮርን ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ በዘጠኝ የአፍሪካ አገራት ላይ የጣለውን ማዕቀብ ተቃወሙ።
- ምዕራብ አውስትራሊያ የደቡብ አውስትራሊያ ኮሮናቫይረስ ደረጃ ከ "ዝቅተኛ" ወደ "መካከለኛ" ከፍ በማለቱ መንገደኞች ወደ ግዛቷ እንዳይዘልቁ አገደች።
- የብሔራዊ ክትባት ጠበብት ቡድን የሶስተኛ ዙር ማጠናከሪያ የኮቪድ ክትባት ከስድስት ወራት ጊዜው ዝቅ እንዳይል ወሰነ።
- የፌዴራል መንግሥቱ ለኮቪድ መከላከያ የሚውል ተጨማሪ $540 ሚሊየን መደበ።
- ታዝማኒያ ከዲሴምበር 15 ጀምሮ የጉዞ ድንጋጌዎቿን ለወጠች
ኮቪድ-19 ስታቲስቲክስ፤
ቪክቶሪያ ውስጥ 1,188 በቫይረስ ሲጠቁ፤ 11 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 337 ነዋሪዎቿ በቫይረስ የተጠቁ ሲሆን፤ የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ አራት፣ ኖርዘርን ቴሪቶሪ ሁለት ሰዎች በቫይረስ ተይዘውባቸዋል።
ወሸባና ገደቦች ክፍለ አገር በክፍለ አገር፤
ጉዞ
የገንዘብ እርዳታ
ሙሉ ክትባት የተከተቡ ነዋሪዎች ቁጥር 70 እና 80 ፐርሰንት በደረሰባቸው ክፍለ ኣገራት የኮቪድ-19 Disaster Payment ይለወጣል፤