- ኒው ሳውዝ ዌይልስ ሙሉ ክትባት ለተከተቡ ዓለም አቀፍ መንገደኞች የቤት ውስጥ ወሸባ ሙከራ እንደምታካሂድ አስታወቀች
- ቪክቶሪያ ከዕኩለ ለሊት በኋላ የተወሰኑ ገደቦቿን ታረግባለች
- የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ውስጥ የአረጋውያን መጠወሪያ ክትባት ግዴታ ሆነ
- ኩዊንስላንድ አንድ ወሸባ ያለ ሰው በቫይረስ መጠቃቱን አስመዘገበች
ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 1,284 ነዋሪዎቿ በቫይረስ ተጠቁ። 12 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። ሕይወታቸውን ካጡት 12 ሰዎች ውስጥ ሁለቱ ወንዶች ዕድሜያቸው 20ዎቹ ውስጥ የነበረ ናቸው። ሶስቱ የዳቦ አረጋውያውያን መጠወሪያ ውስጥ የነበሩ ሲሆን ሰባቱ አልተከተቡም።
የኒው ሳውዝ ዌይልስ እንደራሴ ግላዲስ በርጂክሊያን በTGA ተቀባይነት ያለውን የኮቪድ-19 ክትባት የተከተቡ ዓለም አቀፍ መንገደኞች ለሰባት ቀናት የቤት ውስጥ ወሸባ እንዲገቡ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቁ። የመነሻ ሙከራው የሚከናወነው በ175 መንገደኞች ላይ ሲሆን በዚህ ወር መጨረሻ ላይ ይጀመራል።
ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 510 ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል። የአንድ ሰው ሕይወት አልፏል።
ከዛሬ እኩለ ለሊት አንስቶ ክትባት ያልተከተቡ ወይም የመጀመሪያ ዙር ብቻ የተከተቡ ነዋሪዎች አንድ ከመኖሪያቸው ውጪ ከሆነ ግለሰብ ጋር የእግር ጉዞ ማድረግ ወይም ሽርሽር መሄድ ይችላሉ። ሙሉ ክትባት የተከተቡ ሰዎች ከሁለት መኖሪያ ቤቶች ልጆቻቸው ሳይቆጠሩ እስከ አምስት ሆነው በቡድን የእግር ጉዞ ማድረግ ወይም ሽርሽር መሄድ ይፈቀድላቸዋል።
ከገደቦች መውጫንና እስከ ኖቬምበር ተጥለው የሚቆዩ የገደብ ዓይነቶችን የሚያመላክተውን ፍኖተ ካርታ መንግሥት እሑድ ሴፕቴምበር 19 ይፋ ያደርጋል።
የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ
30 የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ነዋሪዎች በቫይረስ ተይዘዋል።
ከዛሬ ጀምሮ ክትባት ያልተከተቡ የአረጋውያን መጠወሪያ ሠራተኞች የመጀመሪያ የኮቪድ-19 ክትባት እስካልተከተቡ ድረስ ወደ ሥራ ገበታቸው እንዳይመለሱ የተደነገገው ድንጋጌ ግብር ላይ ውሏል።
ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ
- ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ታዝማኒያ ከሪጂናል ኒው ሳውዝ ዌይልስ ለሚመጡ መንገደኞች የ30 ቀናት የቤት ውስጥ ወሸባ ሙከራ ታደርጋለች።
- የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤
NSW and
VIC , and
ACT and
NT and
QLD and
SA and
TAS and
WA and
ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።- ዜናዎችና መረጃዎችን ከ 60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች በመጎብኘት ይመልከቱ።
- ስለ ሚኖሩበት ክፍለ አገር ጠቃሚ መረጃዎችን ከፈለጉ፤ , , , , , , ይጫኑ።
- መረጃዎችን በቋንቋዎ ለማግኘት ይህን ይጫኑ .
በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤
.
የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤
የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤