- ኒው ሳውዝ ዌይልስ ከተጣለው ገደብ ለመውጣት ሶስት ደረጃ ያለውን ፕላን አወጣች
- ቪክቶሪያ የክትባቱን ሂደት ለማፋጠን ለቤተሰብ ሀኪሞች እና መድሃኒት ቤቶች ተጨማሪ የገንዘብ ድጎም አደረገች
- በአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ ለመጀመሪያ ጊዜ አንድ ሰው ህይወቱን አጣ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ
በኒው ሳውዝ ዌይልስ 787 የሚሆኑ ነዋሪዎች በማህበረሰብ ውስጥ በተዛማተ ቫይረስ የተጠቁ ሲሆን 12 ሰዎችም ህይወታቸውን አጥተዋል ፡፡
ፕሪምየር ግላዲስ በርጂክሊያን እንዳረጋገጡትም በአሁን ሰአት ያለው ገደብ ከኦክቶበር 10 በኋላ እንደሚላላ ሲሆን 70% በሚሆነው ፕላኑ ላይ ማሻሻያ ተደርጓል ፡፡ ይሁንና ወደ ሌሎች ከተሞች መንቀሳቀሰን በተመለከተ የተጣለው ገደብ ለጊዜው የሚቆይ ሲሆን ፤ የተከታቢዎቹ ቁጥር 80% እስካልደረሰ ድረስ ባለበት የሚቀጥል ይሆናል ፡፡
ፕሪምየሯ አያይዘው እንደገጹት ገደቦችን ለማላላት የተቀመተው ፕላን በሚያሳየው መሰረት ሁለቱንም ክትባቶች የውሰዱት ሰዎች ቁጥር 80 % ከደረሰም ፤ በሰርግ እና ቀብር ታዳሚዎች ቁጥር ላይ የተቀመጠው ገደብ ፤ እንዲሁም በማህበረሰብ ስፖርቶች ላይ የተጣለው ገደብ ይነሳል ፤ በመኖሪያ ቤቶችም እስከ 10 የሚሆኑ ሰዎች መገኘት ይችላሉ ፡፡
ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 705 ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ የተጠቁ ሲሆን ፤ አንድ ሰው ህይወቱን አጥቷል ፡፡
- ፕሪምየር ዳናኤል አንድሪው የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ ሆኖ የተከታቢዎቹ ቁጥር አነስተኛ በሆኑባቸው አካባቢዎች የክትባቱን ሂደት ለማፋጠን ለቤተሰብ ሀኪሞች እና መድሃኒት ቤቶች ተጨማሪ የገንዘብ ድጎም እንደሚደረግ ይፋ አድርገዋል ፡፡ በዚህም መሰረት ሞርላንድ ፤ ብሪምባንክ ፤ ካርዲኒያ ፤ ኬሲ ፤ ዳረብን፤ ግሬተር ዳንዲኖንግ ፤ ሆብሰን ቤይ ፤ ሜልተን ፤ ዊተልሲ ፤ ዊንድሰር እና ሂውም የገንዘብ ድጎማው ተጠቃሚዎች ናቸው ፡፡
ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ
- የፌዴራል ቱሪዝም ሚኒስትር ዳን ቲሃን መንግሥት የክትባት ፓስፖርትን አካትቶ አስገዳጅ የሆቴል ወሸባ አልባ ዓለም አቀፍ ጉዞን "ቢያንስ ለገና" አምቺ አሠራሮችን ግብር ላይ ለማዋል እየተሰናዳ መሆኑን ገለጡ።
የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤
ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።
- ዜናዎችና መረጃዎችን ከ 60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች በመጎብኘት ይመልከቱ።
- ስለ ሚኖሩበት ክፍለ አገር ጠቃሚ መረጃዎችን ከፈለጉ፤ , , , , , , ይጫኑ።
- መረጃዎችን በቋንቋዎ ለማግኘት ይህን ይጫኑ .
በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤
የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤
የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤