የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ የኒው ሳውዝ ዌይልስ ትምህርት ቤቶች ተከፈቱ

*** ዕድሜያቸው 16 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የቪክቶሪያ ነዋሪዎች ከ89.2 ፐርሰንት በላይ የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ ሲሆን 66.5 ፐርሰንቱ ሙሉ ክትባት ተከትበዋል።

COVID-19 update

Staff welcome students back to school after COVID-19 restrictions were lifted, at Glebe Public School in Sydney. Source: AAP

  • ቪክቶሪያ ለከቤት ውጪ ንግድ የምጣቤ ሃብት መደጎሚያ እንደምትሰጥ አስታወቀች
  • የኒው ሳውዝ ዌይልስ ትምህርት ቤቶች ተከፈቱ
  • ታዝማኒያ በነደፈችው ዕቅድ መሠረት ገደቦቿን ልታነሳ ነው

ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ ውስጥ 1,903 በቫይረስ ተጠቁ፤ ሰባት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።

የሥራ ሚኒስትር ጃላ ፑልፎርድ የአካል እንቅስቃሴ ማጠንከሪያ፣ ችርቻሮ፣ የውበት ሳሎንን ለመሳሰሉ ንግዶችና ድርጅቶች የከቤት ውጪ ንግድ መቋቋሚያ የሚሆን $54 ሚሊየን ዶላርስ የቪክቶሪያ መንግሥት መመደቡን አስታወቁ  

ዕድሜያቸው 16 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የቪክቶሪያ ነዋሪዎች ከ89.2 ፐርሰንት በላይ የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ ሲሆን 66.5 ፐርሰንቱ ሙሉ ክትባት ተከትበዋል።

ሐሙስ ኦክቶበር 21 ዕኩለ ለሊት ላይ ሜልበርንና ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ ተጥለው ያሉ ገደቦች ይረግባሉ። ዓርብ ኦክቶበር 22 ሁሉም ተማሪዎች ወደ መማሪያ ክፍሎቻቸው ይመለሳሉ።

አቅራቢያዎ የሚገኝ የክትባት ማዕከልን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ   

ኒው ሳውዝ ዌይልስ
 ኒው ሳውዝ ዌይልስ 265 ነዋሪዎቿ በቫይረስ ተጠቁ። አምስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። 

ዕድሜያቸው 16 እና ከዚያ በላይ የሆኑ ዘጠና ፐርሰንት ነዋሪዎች የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ ሲሆን 80.3 ፐርሰንቱ ሙሉ ክትባት ተከትበዋል።

በዛሬው ዕለትየ12ኛ ክፍል 1ኛ ክፍልና የሙዋዕለ ሕፃናት ተማሪዎች ወደ መማሪያ ክፍሎቻቸው ከሌሎች ቀደም ብለው ተመለስዋል። የተቀሩት ተማሪዎች በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሳሉ።  

አቅራቢያዎ የሚገኝ የክትባት ማዕከልን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ   

የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ

የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ውስጥ 17 ሰዎች በቫይረስ የተጠቁ ሲሆን 11ዱ የቫይረሱ መስፋፋት ከታወቀባቸው ሥፍራዎች ናቸው።  

ዛሬውኑ የክትባት ቀነ ቀጠሮ ለማስያዝ ይህን ይጫኑ  

ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ

  • ኩዊንስላንድ አንድም በቫይረስ የተያዘ ግለሰብ አላስመዘገበችም።
  • ደቡብ ታዝማኒያና መዲናይቱ ሆባርት በተነደፈላቸው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ዛሬ ምሽት 6pm ላይ የተጣሉባቸው የኮሮናቫይረስ ገደቦች ይነሱላቸዋል። 

Share
Published 18 October 2021 3:46pm
By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends