- የማጠናከሪያ ክትባት ከሁለተኛ ዙር ክትባት ስድስተኛ ወር በኋላ ሊሰጥ ነው
- ቪክቶሪያ የነባር ዜጎች የክትባት መጠንን ከፍ ለማድረግ ጥረቶቿን አደሰች
- ሁሉም የኒው ሳውዝ ዌይልስ ተማሪዎች ዛሬ ወደ ትምህርት ክፍሎቻቸው ተመለሱ
ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ ውስጥ 1,461 በኮቪድ-19 ተጠቁ፤ አንዲት በ20ዎቹ ዓመት ውስጥ ያለች ሴትን ጨምሮ ሰባት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።
የጤና ሚኒስትር ማርቲን ፎሊ በነባር ዜጎች ማኅበረሰባት ዘንድ የክትባት ግንዛቤ ማስጨበጫን ከፍ ለማድረግ ጥረቶች መጨመራቸውን አስታወቁ። በዚህም መሠረት 'ዝቅተኛ ደረጃ' ክትባት ባለባቸው አካባቢዎች ቀጣይነት ያላቸው ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮች ግብር ላይ እንደሚውሉ ገልጠዋል።
ዕድሜያቸው 12 እና ከዚያ በላይ ያሉ የአቦርጂናል ማኅበረሰብ አባላት 80 ፐርሰንት የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ ሲሆን በጠቅላላው ቪክቶሪያ ውስጥ በተመሳሳይ የዕድሜ ፈርጅ ያሉ 90 ፐርሰንት የመጀመሪያ ዙር ክትባት ተከትበዋል።
ከዓርብ ኦክቶበር 29 ጀምሮ ወደ ሪጂናል ቪክቶሪያ መጓዝና ከቤት ውጪ የፊት ጭምብል አለማጥለቅን አካቶ ተጨማሪ ገደቦች ይነሳሉ።
ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 294 ነዋሪዎቿ በቫይረስ ተጠቁ። አራት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።
ሁሉም የኒው ሳውዝ ዌይልስ ተማሪዎች ዛሬ ወደ መማሪያ ክፍሎቻቸው ተመልሰዋል። ይሁንና ከሙሉ ክትባት ግዴታ ጋር ተያይዞ ሁሉም አስተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤቶች አይመለሱም።
“ከ95 ፐርሰንት በላይ መምህራኖቻችን ተከትበዋል። ያም ትምህርት ቤቶቻችን ጥንቃቄን በተላበሰ ሁኔታ ለመክፈት አስችሎናል። እጅጉን የላቀ ጥረት ነው" በማለት እንደራሴ ዶሚኒክ ፔሮቴይ ተናግረዋል።
ሲድኒ ውስጥ ባለፈው ኦገስት በሕዝብና የግል ሆስፒታሎች ታግዶ የነበረው አስቸኳይ ያልሆኑ ቀዶ ሕክምና መሰጠት ተጀምሯል።
ኩዊንስላንድ
ኩዊንስላንድ ዛሬ አንድም በቫይረስ የተጠቃ ግለሰብ አልተመዘገበም።
የክትባት ቀነ ቀጠሮ ለማስያዝ አሁኑኑ ይህን ይጫኑ

Source: Annastacia Palaszczuk
ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ
- የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ 9 ነዋሪዎች በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል።
- ኖርዘር ቴሪቶሪ ለአራት ሳምንታት የሚቆይ የ14 ቀናት የቤት ውስጥ ወሸባ ሙከራ ነገ ይጀምራል።
- የኮቪድ-19 መከላክያ ግብረ ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ጆን ፍሪዌን የአውስትራሊያ ቴክኒካዊ አማካሪ ቡድን ይሁንታን እንዳገኘ ከሙሉ ክትባት ስድስት ወራት በኋላ የማጠናከሪያ ክትባት ዝግጁ እንደሚሆን ገለጡ።
የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤
ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።
- ዜናዎችና መረጃዎችን ከ 60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች በመጎብኘት ይመልከቱ።
- ስለ ሚኖሩበት ክፍለ አገር ጠቃሚ መረጃዎችን ከፈለጉ፤ , , , , , , ይጫኑ።
- መረጃዎችን በቋንቋዎ ለማግኘት ይህን ይጫኑ .
በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤
የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤
የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤