- ኒው ሳውዝ ዌይልስ ውስጥ የቅርቡ ወረርሽኙ መስፋፋት ከጀመረ ወዲህ ከፍተኛ ሬኮርድ ያለው ቁጥር አስመዝግባለች
- ቪክቶሪያ እስካሁን ግኝቱ ያልተፈረጀ አንድ የቫይረስ ጥቃት ላይ ምርመራ እያካሔደች ነው
- ደቡብ አውስትራሊያ ሁለት ሰዎች በቫይረስ ተጠቅተውባታል
- የኩዊንስላንድ ነዋሪዎች ላይ የአንድ ሳምንት የፊት ጭምብል ማጥለቅ ግዴታ ተጣለ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ በዛሬው ዕለት 239 ሰዎች በኮሮናቫይረስ የተጠቁባትና ሁለት ለሕልፈተ ሕይወት የተዳረጉባት መሆኑን አስታወቀች። ሟቿ አረጋዊት ዕድሜያቸው በ90ዎቹ ያለ ሲሆን ሟቹ አረጋዊ ዕድሜያቸው 80ዎቹ ውስጥ የነበረ ነው። ሁለቱም የደቡብ ምዕራብ ሲድኒ ነዋሪዎች ነበሩ። የ126 ተጠቂዎች እንደምን ቫይረሱ እንዳገኛቸው እየተጠና ሲሆን 81ዱ ብቻ ወሸባ ውስጥ ነበሩ።
እንደራሴ ግላዲስ በርጂክሊያን በስምንት ቫይረሱ በተስፋፋባቸው አካባቢዎች ፌይርፊልድ፣ ካንተርበሪ፣ ባንክስታውን፣ ሊቨርፑል፣ ካምበርላንድ፣ ብላክታውን፣ ፓራማታ፣ ካምፕቤልታውንና ጆርጅ ሪቨር ያሉ ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ከአምስት ኪሎ ሜትሮች በላይ ርቀው መሔድ እንደማይችሉ አስታውቀዋል።
ኒው ሳዝ ዌይልስ ውስጥ የፊት ጭምብል ያለማድረግ መቀጮ ክ$200 ወደ $500 ከፍ ተደርጓል። ከነገ ጀምሮ በተደጋጋሚ ሕግ የሚጥሱ ንግድ ቤቶችን የመዝጋት ስልጣን ለፖሊስ ተሰጥቷል።
ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ ውስጥ ስድስት ሰዎች በቫይረስ መጠቃታቸውን በዛሬው ዕለት ተመለከተ። ሁሉም በዴልታ ቫይረስ የተጠቁና ወሸባ ያሉ መሆናቸው ተገልጧል።
የጤና ባለስልጣናት አሁንም ድረስ ትናንት የተከሰተውን የአንድ ቫይረስ ምንጭ ለማጣራት ምርመራ እያካሔዱ ነው።
ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ
- ደቡብ አውስትራሊያ ሁለት ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁባት ሲሆን፤ ሁለቱም ወሸባ ገብተው ያሉ ናቸው።
- በ ነዋሪዎች ለተጨማሪ አንድ ሳምንት የፊት ጭምብል አጥልቀው መቀጠል ግድ ይላቸዋል።
ወሸባ፣ ጉዞ፣ የክሊኒክ ምርመራና የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ
የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤
ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።
- ዜናዎችና መረጃዎችን ከ 60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች በመጎብኘት ይመልከቱ።
- ስለ ሚኖሩበት ክፍለ አገር ጠቃሚ መረጃዎችን ከፈለጉ፤ , , , , , , ይጫኑ።
- መረጃዎችን በቋንቋዎ ለማግኘት ይህን ይጫኑ .
በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤
የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤
የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤