- ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 61 ሰዎች በቫይረስ ተይዘውባታል፤ በመላው ክፍለ አገሪቱ ላይ ገደብ ተጥሏል
- ኒው ሳውዝ ዌይልስ ውስጥ የኮሮናቫይረስ ወረርሽ ከተከሰተ ወዲህ ከፍተኛው በቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ተመዘገበ
- ኩዊንስላንድ አንድም ሰው በቫይረስ ያልተያዘበትን ሁለተኛ ቀን አስቆጠረች
- የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ስምንት ሰዎች በቫይረስ የተጠቁባት ሲሆን አንዳቸውም የማኅበረሰብ ተጋቦት አይደሉም
ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 825 ነዋሪዎቿ በቫይረስ የተጠቁባት መሆኑን በዛሬው ዕለት አስታወቀች፤ የሶስት ሰዎች ሕይወትም አልፏል። ሟቾቹ አንድ 90ዎቹ ውስጥ የነበሩና ያልተከተቡ አረጋዊ፣ አንድ በ80ዎቹ የነበሩ ሙሉ ክትባት የተከተቡና አንዲት በ90ዎቹ ዕድሜ ያሉና አንድ ጊዜ ብቻ የተከተቡ አረጋዊት ይናቸው።
ቫይረስ ተስፋፍቶ ባለባቸው የአካባቢ መንግሥት ሥፍራዎች ነዋሪ ሆነው ዕድሜያቸው ከ16 እስከ 39 ያሉ ግለሰቦች የኮቪድ-19 ፋይዘር ቀጠሮ አስይዘው መከተብ ይችላሉ።
ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 61ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል። 39ኙ ወሸባ ገብተው ያሉ ናቸው።
ሪጂናል ቪክቶሪያ ውስጥ በርካታ ሰዎች በቫይረስ መያዝን ተከትሎ ከዛሬ 1pm ጀምሮ ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ ገደብ ተጥሏል።
ከሰዓት ዕላፊ በስተቀር ሜልበር ላይ ተጥለው ያሉት ገደቦች በሙሉ ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ የፀኑ ይሆናሉ።
የመመርመሪያ ጣቢያዎችን ማወቅ ከፈለጉ ይህን ይጫኑ በአቅራቢያዎ የሚገኙ የክትባት ማዕከላትን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ .
ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ
- የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ስምንት ነዋሪዎች በኮቪድ-19 መጠቃትን ተከትሎ ዕድሚያቸው ከ12 ዓመት ጀምሮ ያሉ ታዳጊ ወጣቶችን በዚህ ዓመት መጨረሻ ለመከተብ ዕቅድ ተይዟል።
- ኩዊንስላንድ ለሁለት ተከታታይ ቀናት አንድም ሰው በቫይረስ ያልተያዘባት ሲሆን ከ16 ዓመት በላይ ያሉ ነዋሪዎቿ እንዲከተቡ ባለ ስልጣናት ጥሪ አቅርበዋል።
- የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤
ወሸባ፣ ጉዞ፣ የክሊኒክ ምርመራና የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ
NSW and
VIC , and
ACT and
NT and
QLD and
SA and
TAS and
WA and
ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።- ዜናዎችና መረጃዎችን ከ 60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች በመጎብኘት ይመልከቱ።
- ስለ ሚኖሩበት ክፍለ አገር ጠቃሚ መረጃዎችን ከፈለጉ፤ , , , , , , ይጫኑ።
- መረጃዎችን በቋንቋዎ ለማግኘት ይህን ይጫኑ .
በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤
.
የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤
የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤