- የኒው ሳውዝ ዌይልስ እንደራሴ አሳሳቢ የአካባቢ መንግሥት ክፍለ ከተሞች ላይ ተጥለው የነበሩ ገደቦች መርገባቸውን አስታወቁ
- ቪክቶሪያ ከገደቦች የመውጫ ፍኖተ ካርታዋን ይፋ አደረገች
- የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ 17 ነዋሪዎች በኮቪድ-19 ተጠቁ
- ኩዊንስላንድ በአንድ ቀን ውስጥ አዲስ የክትባት ሬኮርድ አስመዘገበች
ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 1,083 ነዋሪዎቿ በቫይረስ ተጠቁ። 13 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።
እንደራሴ ግላዲስ በርጂክሊያን ከሰኞ ሴፕቴምበር 20 ጀምሮ ሁሉም የአሳሳቢ አካባቢ መንግሥት ክፍለ ከተሞች ከተቀረው የሲድኒ ክፍለ ከተሞች ጋር በተመሳሳይ ድንጋጌ ስር እንደሚሆኑ አስታወቁ። ፈቃድ ያላቸው ሠራተኞችና የጉዞ ፈቃድ መመሥፈርቶች ፀንተው የሚቆዩ እንደሆነም አሳስበዋል
በመላው ኒው ሳውዝ ዌይልስ ከቤት ውጭ ያሉ የመዋኛ ሥፍራዎች የኮቪድ-ጥንቃቄ ፕላን ይሁንታ ያላቸው በመሆኑ ከሰኞ ሴፕቴምበር 27 አንስቶ ግልጋሎት መስጠት ይጀምራሉ።
በአሁኑ ወቅት የክትባት መመዘኛዎችን ከሚያሟሉ የኒው ሳውዝ ነዋሪዎች ውስጥ 81.9 ፐርሰንት የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ ሲሆን 51.9 ፐርሰንት ሙሉ ክትባት ተከትበዋል።
ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 507 ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል። የአንድ ሰው ሕይወት አልፏል።
እንደራሴ ዳንኤል አንድሩስ ባለ አምስት ደረጃ ከገደቦች መውጫ ፍኖተ ካርታ ይፋ አደረጉ። እንደታሰበው ኦክቶበር 26 የክትባት መመዘኛዎችን ከሚያሟሉት ውስጥ 70 ፐርሰንት የቪክቶሪያ ነዋሪዎች ሙሉ ክትባት ከተከትቡ ተጥለው ያሉ ገደቦች እንዲያከትሙ ይደረጋል።
አቶ አንድሩስ ዕቅዱን አስመልክተው "ዳግም ክፍት እንሆናለን፤ ወደ ኋላ መመለስ አይኖርም" ብለዋል። የ80 ፐርሰንት ሙሉ ክትባት የተያዘለትን ዕቅድ ከመታ በገና ዕለት እስከ 30 እንግዶችን በቤት ውስጥ ማስተናገድ ይቻላል።
ዳታዎች እንደሚያመለከቱት ከሆነ 71.2 ፐርሰንት ያህል የክትባት መመዘኛዎችን ከሚያሟሉ የቪክቶሪያ ነዋሪዎች የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ-19 ክትባቶችን፤ 43.5 ፐርሰንት ሙሉ ክትባቶችን ተከትበዋል።
ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ
- የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ 17 ነዋሪዎች በቫይረስ ተጠቅተዋል፤ 12ቱ የማኅበረሰብ ተጋቦት ናቸው።
- በትናንትናው ዕለት 31,004 የኩዊንስላንድ ነዋሪዎች ክትባት በመከተብ አዲስ ሬኮርድ አስመዝግበዋል። ከተከታቢዎቹ ውስጥ 59.34 ፐርሰንቱ የመጀመሪያ ዙር ተከታቢዎች ናቸው።
- የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤
NSW and
VIC , and
ACT and
NT and
QLD and
SA and
TAS and
WA and
ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።- ዜናዎችና መረጃዎችን ከ 60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች በመጎብኘት ይመልከቱ።
- ስለ ሚኖሩበት ክፍለ አገር ጠቃሚ መረጃዎችን ከፈለጉ፤ , , , , , , ይጫኑ።
- መረጃዎችን በቋንቋዎ ለማግኘት ይህን ይጫኑ .
በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤
.
የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤
የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤