የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ ቪክቶሪያ ተጨማሪ ገደቦችን ልታነሳ ነው

*** የአውስትራሊያ ስታቲስቲክስ ቢሮ ባሕር ማዶ የተወለዱ ሰዎች የኮቪድ-19 የሞት መጠን ከ100,000 ሰዎች ውስጥ 4.2 ሲሆን፤ አውስትራሊያ የተወለዱ 2.0 መሆኑን ገለጠ።

COVID-19 update

Melbourne's CBD is seen from the banks of Williamstown. Source: AAP

  • ቪክቶሪያውያን ዛሬ የሚነሱ ገደቦችን እየጠበቁ ነው
  • የኒው ሳውዝ ዌይልስ ባለስልጣናት ነዋሪዎች ሃለዊንን የኮቪድ-ጥንቃቄ በተመለበት መንገድ እንዲያከብሩ አሳሰቡ
  • ቪክቶሪያ የኮቪድ-19 ክትባት ያለመከተብን አስባቦችን እያጠበቀች ነው

 ቪክቶሪያ

ቪክቶሪያ ውስጥ 1,656 ነዋሪዎች በኮቪድ-19 ተጠቁ፤ 10 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። ቪክቶሪያ ዛሬ ከምሽቱ 6 pm ጀምሮ ተጨማሪ ገደቦችን ታነሳለች።

በጣም አስፈላጊ ያልሆኑ ችርቻሮዎች ከሳምንታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ይከፈታሉ፤ ምግብ ቤቶች፣ መጠጥ ቤቶችና ካፌዎች የመስተንግዶ አቅማቸው ይጨምራል።   

በሜልበርና ሪጂናል ቪክቶሪያ መካከል ተጥሎ የነበረ የጉዞ ገደብ ያከትማል። በመላ ቪክቶሪይ የመዘዋወር እገዳ አይኖርም። የሪጂናል ቪክቶሪያ ነዋሪዎች ለሜልበርን ዋንጫ ወደ ሜልበርን ከተማ መምጣት ይችላሉ። 

የፊት ጭምብል የማጥለቅ ግዴታ አይኖርም፤ ሆኖም ርቀትን መጠበቅ በማይቻልባቸው የቤት ውስጥ ኩነቶች የፊት ጭምብል የማጥለቅ ግዴታ ይኖራል።  

አቅራቢያዎ የሚገኝ የክትባት ማዕከልን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ   

ኒው ሳውዝ ዌይልስ
 ኒው ሳውዝ ዌይልስ 268 ነዋሪዎቿ በቫይረስ ተጠቁ። ሁለት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። 

በዚህ ሳምንት መጨረሻ ሃለዊን የኮቪድ-ጥንቃቄ በተመለበት ሁኔታ ማክበር ይቻላል። ለልጆች የሚሰጡ ከረሜላዎች የታሸጉ መሆን ይገባቸዋል።

የክትባት ቀነ ቀጠሮ ለማስያዝ አሁኑኑ ይህን ይጫኑ  

ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ

  • የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ 10 ነዋሪዎች በቫይረስ መጠቃታቸውን መዝግባለች፤ በጠቅላላው 234 ነዋሪዎች በቫይረስ ተጠቅተዋል።  
  • የአውስትራሊያ ስታቲስቲክስ ቢሮ ባሕር ማዶ የተወለዱ ሰዎች የኮቪድ-19 የሞት መጠን ከ100,000 ሰዎች ውስጥ 4.2 ሲሆን፤ አውስትራሊያ የተወለዱ 2.0 መሆኑን ገለጠ።
  • ሰዎች የኮቪድ-19 ክትባት ላለመከተብ ሐኪሞች ዘንድ እየሄዱ የሕክምና ማስረጃ እንዲሰጣቸው የመጠየቅ አስባቦች መበርከትን ተከትሎ የቪክቶሪያ መንግሥት ደንቦችን እያጠበቀ ነው። 
የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤

ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ . ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ  ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።





በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤

የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤


 
 

የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤

 
 
 

 

 

 



Share
Published 29 October 2021 1:44pm
Updated 29 October 2021 1:50pm
By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends