- ከዛሬ ጀምሮ ወደ አውስትራሊያ የሚመጡ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችና የሥራና ሽርሽር ባለቪዛዎች ለቪዛ የፈጸሙት ክፍያ ተመላሽ ይሆንላቸዋል፤ ይህ የሚሆነውም ሌሎችም ወደ አውስትራሊያ ፈጥነው እንዲመጡ ለማበረታት ነው
- ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የተደረጉት ለውጦች በኦሚክሮን መዛመት ሳቢያ አገሪቱን ገጥመዋት ያሉትን የሠራተኛ ኃይል እጥረቶች ለመግታት እንደሆነ አስታውቀዋል
- ክፍያዎቹ ነፃ ሆነው የሚቆዩት ከረቡዕ ጀምሮ በስምንት ሳምንታት ውስጥ ለሚዘልቁ ዓለም አቀፍ ተማሪዎች፤ እንዲሁም ለሥራና ሽርሽር ባለቪዛዎች እስከ 12 ሳምንታት ባሉት ጊዜያት ይሆናል
- ሶስት በርካታ ነዋሪዎች በሚኖሩባቸው የአውስትራሊያ ክፍለ አገራት ውስጥ 61 ሰዎች በኮቪድ-19 ተጠቅተው ሕይወታቸውን አጥተዋል
- ኒው ሳውዝ ዌይልስ ውስጥ 32 ሰዎች ለሞት ሲዳረጉ ሆስፒታል ከሚገኙት 2,863 ሕሙማን ውስጥ 217 በፅኑዕ ሕሙማን ክፍል ይገኛሉ
- ፕሪሚየር ዶሚኒክ ፐሮቴይ ከዛሬ ጀምሮ ሁለተኛ ክትባታቸውን ከተከተቡ ሶስት ወይም ከዚያ በላይ ወራት የሞላቸው የኒው ሳውዝ ዌይልስ ነዋሪዎች የሶስተኛ ዙር ክትባታቸውን መከተብ እንደሚችሉ አስታውቀዋል
- የአውስራሊያ ዋና የሕክምና መኮንን ፕሮፌሰር ፖል ኬሊ መጪው ክረምት እንደ ጉንፋን ከመሳሰሉ ዓመታዊ ተላላፊ በሽታዎች ጋር ተዳምሮ የኮሮናቫይረስ እንዲያገረሽና አዲስ ቫይረስም እንዲከሰት ሊያደርግ እንደሚችል አመላከቱ
- ኩዊንስላንድ ከቅዳሜ 1am ጀምሮ ሁለት ዙር ክትባት ለተከተቡ ዓለም አቀፍ መንገደኞች ወሸባ መግባት እንዲቀርላቸው ልታደርግ ነው
- ፕሪሚየር አናስታዥያ ፓለሼይ ቀኑ የተመረጠው የከፍለ አገሪቱ ሁለት ዙር ተከታቢዎች ቁጥር በመጪዎቹ ቀናት 90 ፐርሰንት ስለሚደርስ መሆኑን ገልጠዋል
- የሜልበርን አውሮፕላን ማረፊያ ሁለት ዙር ክትባት ለተከተቡ ዓለም አቀፍ መንገደኞች የቅድመ በረራ የኮሮናቫይረስ ምርመራ እንዲቀር ጥሪ አቀረበ፤ እስካሁን በአለው አሠራር መንገደኞች ከጉዟቸው ሶስት ቀናት ቀደም ብሎ ከቫይረስ ነፃ መሆናቸውን የሚያሳይ የPCR ምርመራ ውጤታቸውን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል
የተለያዩ ከፍለ አገራት የፈጣን አንቲጄን ምርመራ መመዝገቢያ ቅጾች፤
ኮቪድ-19 ስታቲስቲክስ፤
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 32,297 ነዋሪዎቿ በቫይረስ የተጠቁ ሲሆን፤ የ32 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
ቪክቶሪያ ውስጥ 20,769 በቫይረስ ሲጠቁ፤ 18 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ኩዊንስላንድ 19,932 ነዋሪዎች በቫይረስ ሲያዙ፣ 11 ሰዎች ለሕልፈተ ሕይወት ተዳርገዋል።
ታዝማኒያ 1,185 ሰዎች ተጠቅቶባታል።
ወሸባና ገደቦች ክፍለ አገር በክፍለ አገር፤
ጉዞ
የገንዘብ እርዳታ
ሙሉ ክትባት የተከተቡ ነዋሪዎች ቁጥር 70 እና 80 ፐርሰንት በደረሰባቸው ክፍለ ኣገራት የኮቪድ-19 Disaster Payment ይለወጣል፤
- ከ60 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ዜናዎችና መረጃዎች ከ
- የክፍለ አገርዎ ረብ ያላቸው መምሪያዎች , , , , , , .
- ስለ ኮቪድ-19 መረጃ በቋንቋዎ