የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤የዓለም ጤና ድርጅት ኦሚክሮን ቫይረስን በተመለከተ ከልክ ያለፉ ገደቦች እንዳይጣሉ አሳሰበ

*** የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከዳር እስከ ዳር የሚጣሉ ድፍን እገዳዎች የኦሚክሮንን መስፋፋት ከመግታት ይልቅ ከቶውንም በሰዎች 'ሕይወት ላይ ጫናን እንደሚያሳድር' አሳሰቡ። ቫይረሱ በአሁኑ ወቅት 23 አገራት ውስጥ ተሰራጭቶ ይገኛል።

WHO director-general Tedros Ghebreyesus says its too early to relax

WHO director-general Tedros Ghebreyesus says its too early to relax Source: AAP

  • የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከዳር እስከ ዳር የሚጣሉ ድፍን እገዳዎች የኦሚክሮንን መስፋፋት ከመግታት ይልቅ ከቶውንም በሰዎች 'ሕይወት ላይ ጫናን እንደሚያሳድር' አሳሰቡ። ቫይረሱ በአሁኑ ወቅት 23 አገራት ውስጥ ተሰራጭቶ ይገኛል። 
  • ድርጅቱ ለተላላፊ በሽታ ከፍተኛ ተጋላጭነት ያላቸው ሰዎች ጉዟቸውን ቢገቱ የተሻለ እንደሚሆን አመላካች መምሪያ አውጥቷል። 
  • ኒው ሳውዝ ዌይልስ ውስጥ ሰባተኛ ሰው በኦሚክሮን መጠቃቱ ተገለጠ። ግለሰቡ ደቡብ አፍሪካ እንዳልነበረም ተነግሯል። 
  • የቪክቶሪያ ጤና ሚኒስትር ኦሚክሮን ማኅበረሰቡ ውስጥ ሳይዘልቅ እንዳልቀረ ጠቆሙ። እስካሁን ድረስ ቪክቶሪያ ውስጥ በቫይረሱ የተያዘ ሰው አልተመዘገበም። 
  • የቪክቶሪያ ፕሪሚየር ክትባት የተከተቡ ሰዎች ቁትር ከፍተኛ በመሆኑ በኮቪድ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እምብዛም እንደማያሳስብ ተናገሩ። 
  • የኩዊንስላንድ ፕሪሚየር አንስታዥያ ፓለሼይ ትናንት ጎልድ ኮስት ውስጥ በኮሮናቫይረስ መያዙ የተረጋገጠው ግለሰብ በጥቁር ዓርብ ዕለት በርካታ ቦታዎች መዘዋወሩን ገለጡ። 

ኮቪድ-19 ስታቲስቲክስ፤

ቪክቶሪያ ውስጥ 1,419 በቫይረስ ሲጠቁ፤ 10 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።  

ኒው ሳውዝ ዌይልስ 271 ነዋሪዎቿ በቫይረስ የተጠቁ ሲሆን፤ የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ስምንት፣ ኖርዘርን ቴሪቶሪ አንድ ሰው በቫይረስ የተጠቃባቸው መሆኑን መዝገበዋል።  

 


ወሸባና ገደቦች ክፍለ አገር በክፍለ አገር፤

ጉዞ

 የኮቪድ-19 እና የጉዞ መረጃ 

የገንዘብ እርዳታ

ሙሉ ክትባት የተከተቡ ነዋሪዎች ቁጥር 70 እና 80 ፐርሰንት በደረሰባቸው ክፍለ ኣገራት የኮቪድ-19 Disaster Payment ይለወጣል፤  


 

 





 

 


Share
Published 2 December 2021 6:14pm
Updated 2 December 2021 6:23pm
By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends