አውስትራሊያ በአዲሱ ኦሚክሮን ኮቪድ-19 ሳቢያ ዓለም አቀፍ ድንበሮቿን የመክፈቻ የጊዜ ሠሌዳ በሁለት ሳምንት አራዘመች

*** ቀደም ብሎ በተያዘው ዕቅድ መሠረት 200,000 ሠራተኞችና ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ወደ አውስትራሊያ ከረቡዕ ዲሴምበር 1 ጀምሮ መዝለቅ ይጀምሩ ነበር።

COVID-19 update

International travellers wearing personal protective equipment (PPE) arrive at Melbourne's Tullamarine Airport on November 29, 2021. Source: AAP

የአውስትራሊያ ፌዴራል መንግሥት የዓለም አቀፍ ድንብሮቹን የመክፈቻ ጊዜ ከዲሴምበር 1 ወደ ዲሴምበር 15 አሸጋገረ።

የጤና ሚኒስትር ግሬግ ሃንት ለዓለም አቀፍ ድንበሮቹ መከፈቻ ጊዜ ለ14 ቀናት እንዲገታ የተደረገው በኦሚክሮን ኮቪድ-19 ሳቢያ እንደሆነ አመላክተዋል።

ቀደም ብሎ በተያዘው ዕቅድ መሠረት 200,000 ሠራተኞችና ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ወደ አውስትራሊያ ከረቡዕ ዲሴምበር 1 ጀምሮ መዝለቅ ይጀምሩ ነበር።   

የጉዞ ገደቡ ከጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የሚመጡ ሙሉ ክትባት የተከተቡ መንገደBኦችንም ይመለከታል። 


Share
Published 30 November 2021 11:52am
Updated 30 November 2021 12:04pm
By NACA

Share this with family and friends