ኒው ሳዝ ዌይልስ በዛሬው ዕለት 97 ሰዎች በኮሮናቫይረስ ተይዘዋል።
የሲድኒ የኮሮናቫይረስ ገደብም ለተጨማሪ ሁለት ሳምንታት እስከ ጁላይ 30 እንዲራዘም መወሰኑን ፕሪሚየር ግላዲስ በርጂክሊያን አስታወቁ።
ወ/ሮ በርጂክሊያን የተጣሉትን ገደቦች ከመነሳታቸው በፊት በሁለቱ ሳምንታት ውስጥ የቫይረሱን መስፋፋት መጠን አስመልክቶ ግምገማ እንደሚደረግ ገልጠዋል።
የጤና ባለ ስልጣናት የፌርፊልድ ነዋሪዎች ከቤት እንዳይወጡ፤ የካንተርበሪና ሊቨርፑል ነዋሪዎችም እንቅስቃሴያቸውን እንዲገድቡ አሳስበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 7 ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን አስታውቃለች።
በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ ስድስቱ ከኒው ሳውዝ ዌይልስ የቤት ዕቃ አጓጓዦች ጋር በነበራቸው ንኪኪ የተጠቁ ሲሆን አንደኛው ግለሰብ ከሲድኒ ወደ ሜልበርን የተመለሰ ነው።