በአለም አቀፍ ዙሪያ የሚገኙ ሆስፒታሎች የኦሚኮርን መስፋፋት ተከትሎ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ናቸው ተባለ ።
የመስኩ ባለሙያዎች እንዲሚናገሩት ከሆነ የተጨማሪ ማጠናከሪያ ከትባት (ቡስተር) ፤ ሆስፒታል ሊገቡ የሚችሉ ህሙማንን ቁጥር በመቀንስ ረገድ ያለው አስተዋትጻኦ ከፈፍኛ መሆኑን ነው ። አያይዘውም ተጨማሪ የቫይረስ አይነቶች እንደሚመጡም መጠበቅ ግድ ነው ብለዋል ።
እንግሊዘ ወደ ጠንካራው ብርዳማ ወቅት እይሄደች ባለችበት እና የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎች በጨመሩብት ወቅት ፤ በአንጻሩ የማቾች ቁጥን ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር እጅግ ዝቅ ያለ ነው። ይህም የክትባቱን ውጤታማነት አንዱ ማሳያ ነው ተብሏል።
ለንደን በሚገኘው በሮያል ፍሪ ሆስፒታል ከፍተኛ እንክብካቤ የሚያሻቸው ህሙማን በሚቆዩበት ክፍል ውስጥ ካሉ የኮሮናቫይረስ ህሙማን መካከል ግማሽ ያህሉ ሁለቱን ክትባቶች ያልወሰዱ ናቸው።
በአሁን ሰአትም 19,000 የሚሆኑ የኮቪድ-19 ህሙማን ሲኖሩ ፤ ባላፈው የሪፕርት ወቅት ላይ 398 ሰዎች ህይወታቸውም ማጣታሽቸው ተገልጿል ።
በተያያዥም በፈረንሳይ በዚህ ሳምንት በአንድ ቀን ብቻ 368,000 ስዎች መያዛቸው የተገለጸ ሲሆን ፤ በጣልያን ባለፈው ማክሰኞ 220,532 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል ።
የጀርመኑ ቻንስለር አህላፍ ሾልዝ በፓርላማ ንግግራቸው የኮቪድ-19 በመላው አገሪቱ በግዴታ መውሰድ እንዳለበት ተናግረዋል። በጀርመ 83፣430 አዲስ የኮቪድ ተያዦችን ቁጥር ተመዝግቧል ።
በአሜሪካ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች በአንድ ቀን ብቻ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሲሆን ፤ ቁጥሩም የአለማችን ከፍተኛው አንደሆነ ተነግሮለታል ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የመስኩ ሳይንቲስቶች ኦሚኮርን ቫርያንት የመጨርሻው አይነት ቫይረስ እንደማይሆን እና ሌሎችም ተጨማሪ የቫይረስ አይነቶች ሊመጡ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል ።