ቪክቶርያ ባላፉት 24 ሰአታት 12 አዲስ የኮሮናቫይረስ ተያዦችን ቁጥርን አስመዘገበች የተጣሉት ገደቦች ቀስ በቀስ እንደሚላሉ ዳንኤል አንድሪውስ ቃል ገቡ

ቪክቶርያ ባለፉት 24 ሰአታት 12 አዲስ የኮሮናቫይረስ ተያዦችን ቁጥር ያስመዘገበች ሲሆን ከአረጋውያን መጦሪያ ቤቶች ጋር በተያያዘም ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

Victorian Premier Daniel Andrews addresses the media during a press conference in Melbourne, Thursday, September 24, 2020. Victoria has recorded 12 new cases and two deaths in the past 24 hours. (AAP Image/James Ross) NO ARCHIVING

Victorian Premier Daniel Andrews addresses the media. Victoria has recorded 12 new cases and two deaths in the past 24 hours. Source: AAP

ቪክቶርያ ባለፉት 24 ሰአታት 12 አዲስ የኮሮናቫይረስ ተያዦችን ቁጥር ያስመዘገበች ሲሆን ከአረጋውያን መጦሪያ ቤቶች ጋር በተያያዘም ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

በለፉት 14 ቀናት በተሰበሰቡት መረጃዎች መሰረት የተያዦች ቁጥር በተከታታይ መቀነስን አሳይቷል ፡፡

ቁጥሮቹም ከ 30 እስክ 50 ባሉት ውስጥ በመሆናቸውም ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የተጣሉ ገደቦችን ለማላላት እንደሚያስችል ተነግሯል፡፡

የቪክቶርያው ፕሪምየር ዳንኤል አንድሪውስ በተቀመጠው ፍኖተ ካርታ መሰረት ቪክቶርያ ወደ ደረጃ 2 ለመሸጋገር በጥሩ መስመር ላይ ነች ብለዋል ፡፡

አያይዘውም “ በመጪው እሁድ ከፍተኛ የሚባል እርምጃ የምንወስድበት ላይሆን ይችላል ፤ ፍኖተ ካርታውም ይህንን አይፈቅድም ነገር ግን ቀስ በቀስ ጥንቃቄን እና ተከታታይነትን በተሞላ መልኩ ነው እንዲከናወን የምንፈልገው ፤ ምክንያቱም መቀነሱም የታየው ቀስ በቀስ እና ተከታታይ በሆነ መልኩ ነው ብለዋል፡፡ ’’


Share
Published 24 September 2020 3:50pm
By SBS News
Presented by Martha Tsegaw
Source: SBS

Share this with family and friends