በቪክቶሪያ 57 ሰዎች በማህበረሰብ ውስጥ በተዛመተ የኮሮናቫይረስ ተጠቁ

Victorian Premier Daniel Andrews addresses the media during a press conference in Melbourne

Victorian Premier Daniel Andrews addresses the media during a press conference in Melbourne Source: AAP

በቪክቶሪያ 57 ሰዎች በማህበረሰብ ውስጥ በተዛመተ የኮሮናቫይረስ ተጠቁ ።

ይህ ቁጥርም የሁለተኛው ዙር የቫይረስ ስርጭት ከታየ በኋላ ከፍተኛ የሚባል እንደሆነ ተነግሯል ።

የጤና ዲፓርትመንት እንዳሳወቀው አዲስ ከተመዘገቡት ውስጥም 54ቱ በቅርቡ ከታየው ወረርሽኝ ጋር የሚገናኙ ሲሆን 42 ያህሉም ራሰቸውን ለይተው ያስቀመጡ ናቸው ።የተቀሩቱ ሶስቱ ምንጫቸው እስካሁንም  አልታወቀም ።

የቪክቶሪያው ፕሪምየር ዳናኤል አንድሪውስ እንዳሉት ከ 44 ቱ ውስጥ 41 ያህሉ በሚያስተላልፉበት ወቅት በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆን በ13ተኛ ቀናቸውም እንደገና ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።

ስለሆነም ሁሉም እንደገና ራሳቸውን ለይተው ማቆየት ይኖርባቸዋል ብለዋል ።    


Share
Published 19 August 2021 6:14pm
By Stephanie Corsetti
Presented by Martha Tsegaw

Share this with family and friends