አፍሪካ በኮቪድ - 19 ሳቢያ 190,000 ሕይወቶች ሊቀጠፉባት 44 ሚሊየን ሊጠቁባት ይችላሉ - የዓለም ጤና ድርጅት

የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ባደረገው አዲስ የጥናት ሞዴል የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን አፍሪካ ውስጥ በቅጡ መቆጣጠር ካልተቻለ በአኅጉሪቱ ላይ የከፋ ጉዳት እንደሚያደርስ አሳስቧል።

WHO says coronavirus could kill 190,000 in Africa if containment measures fail

Lagos food markets reopened this week after a five-week lockdown in the Nigerian capital. Source: EPA

የዓለም ጤና ድርጅት የኮቪድ - 19 ወረርሽኝን በውል መከላከል ካልተቻለ በወረርሽኙ የመጀመሪያ ዓመት እስከ 190,000 ያህል ሰዎች ሕይወት ሊቀጠፍ እንደሚችል አስጠንቅቋል። 

የተባበሩት መንግሥታት የጤና ኤጀንሲ የብራዛቪል ቢሮ ጥናት እንዳመለከተው ከሆነ በኮሮናቫይረስ ከ 83,000 እስከ 190,000 አፍሪካውያን ለሞት ሊዳረጉ እንደሚችሉና ከ 29 እስከ 44 ሚሊየን የሚደርሱቱ የቫይረሱ ተጠቂዎች እንደሚሆኑ አመልክቷል።

ምርምሩ መሠረቱን ያደረገው 47 አገራትንና አንድ ቢሊየን ሰዎችን ባካተተ የትንበያ ሞዴል መሆኑን የጤና ድርጅቱ መግለጫ ጠቁሟል።
WHO says coronavirus could kill 190,000 in Africa if containment measures fail
Shoppers at a Nigerian fish market wear face masks to prevent the spread of COVID-19. Source: AP
የጤና ጠበብቱ አፍሪካ በተለይ በደካማ የጤና መሠረተ ልማቷ፣ ከፍተኛ የድህነት መጠን፣ በርካታ ግጭቶችና ወረርሽኞችን የመጠራጠር የቀደምት ተሞክሮዎቿ ተደራርበው ለወረርሽኙ ተጋላጭነቷን እንደሚያጎላው አመላክተዋል። 

የቫረሱ አፍሪካ ውስጥ ተዛማችነት ግና በአውሮፓ፣ ዩናይትድ ስቴትስና ሌሎች አገራት የተከሰተውን ያህል ያሻቀበ ሳይሆን ያዘገመ ነው።

የአፍሪካ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ማትሺዲሶ ሞቲ የቫይረሱን አፍሪካ ውስጥ ማዝገም አንስተው ሲናገሩ "ዝቅተኛ ተዛማችነቱ የሚያመለክተው ወረርሽኙ ለጥቂት ዓመታት የሚቆይ መሆኑን ነው። ምንም እንኳ አሁን 50 000 በቫይረሱ ተጠቅተዋል 2000 ሕይወታቸውን አጥተዋል ቢባልም፤ ቫይረሱን ለመመከት አገራት ዳታን መሠረት ያደረገ ተጨባጭ መረጃን መጠቀም ያሻቸዋል" ብለዋል።  

ትናንሽ አገራትን አክሎ አልጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካና ካሜሩን በተለይ ለቫይረሱ በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ በመሆናቸው ብርቱ የመከላከል እርምጃዎችን ሊወስዱ እንደሚገባ የዓለም ጤና ድርጅት አሳስቧል።

እስካሁን ድረስ አፍሪካ ውስጥ 53,334 በቫይረሱ የተጠቁና 2,065 ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን፤ በመላው ዓለም 267,000 ያህል ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል።

በርካታ የአፍሪካ አገራት የተለያዩ ቅድመ መከላከል እርምጃዎችን ወስደዋል። የተወስኑቱ የጣሏቸው ገደቦች ጸንተው ያሉ ሲሆን ናይጄሪያና ደቡብ አፍሪካ ባለፈው ሳምንት ገደቦቻቸውን አላልተዋል።


Share

Published

By NACA
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends