ከታህሳስ 4 እስከ 6 ተካሒዶ የተጠናቀቀው የዩናይትድ ስቴትስና አፍሪካ አገራት መሪዎች ጉባኤ ላይ 49 የአፍሪካ አገራት መሪዎች ተጋብዘዋል። ጉባኤው መሠረቱን ያደረገውም በጋራ መከባበር፣ የጋርዮሽ ጥቅሞችና ዕሴቶችን መርህ እንደነበር ተመልክቷል።
ጉባኤውን በንግግር የዘጉት የአስተናጋጇ አገር ዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን "የአፍሪካውያን ድምፆች፣የአፍሪካውያን አመራር፣ የአፍሪካውያን ፈጠራ" አንገብጋቢ ሉላዊ ችግሮችን በመክላት የጋራ ርዕዮቻችን የሆኑትን ነፃ፣ ግልፅ፣ የበለፀገችና ደህንነቷ የተጠበቀ ዓለም ዕውን ለማድረግ ወሳኝ እንደሆኑ አመላክተዋል።
አፍሪካ በእያንዳንዱ ሉላዊ ተግዳሮቶች ላይ ውይይቶች በሚካሔድበት ክፍል ጠረጴዛ ዙሪያና ተቋማት ውስጥ ውክልና ሊኖራት እንደሚገባ እንደሚያምኑ በመግለጽ፤ በመስከረሙ የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ ወቅትም ዩናይትድ ስቴትስ የተመድ ፀጥታ ምክር ቤት ክለሳን ሙሉ ለሙሉ እንደምትደግፍና አፍሪካም ቋሚ ውክልና እንዲኖራት አቋማቸውን ያንፀባረቁ መሆኑን አውስተዋል።
ያንንም ተከትሎ፤ በዕለቱ የአፍሪካ ኅብረት በቡድን 20 ቋሚ አባልነት እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
አክለውም፤ ከዩናይትድ ስቴት ስ ኮንግረስ ጋር በቅርብ ትብብር በመሥራት 55 ቢሊየን ዶላርስ በመመደብ የአፍሪካን 2063 ቀዳሚ አጀንዳ ወደፊት ለማራማድ እንዲያስችል መወጠኑን ጠቁመዋል። ይህም ለአፍሪካ ሕዝብ፣ ለአፍሪካ መሠረተ ልማት፣ ለአፍሪካ ግብርና፣ ለአፍሪካ ጤና ሥርዓትና ለሌሎችም ተግባራት የሚውል መሆኑን ፕሬዚደንቱ አመላክተዋል።
እንዲሁም፤ኮንግረስ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ላላቸው አገራት መደጎሚያነት የሚውል 21 ቢሊየን ዶላርስ ለዓለም አቀፉ ገንዘብ ድርጅት ለማበደር ይሁንታውን እንዲቸር መጠየቃቸውን ተናግረዋል።

U.S. President Joe Biden speaks during the Leaders Session – Partnering on Agenda 2063 at the U.S. - Africa Leaders Summit on December 15, 2022 in Washington, DC. The Summit brings together heads of state, government officials, business leaders, and civil society to strengthen ties between the U.S. and Africa. Credit: Kevin Dietsch/Getty Images
በሌላም በኩል፤ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ እንዳስታወቀው የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የጤና አገልግሎቶችና የጎርፍ ፕሮጄክቶች ሥራ ማስፈፀሚያ የሚሆን 745 ሚሊየን ዶላር መፍቀዱን ገልጧል።
ፕሬዚደንት ባይደን ለአፍሪካውያኑ መሪዎችና ቀዳማዊት እመቤቶች በዋይት ሐውስ የእራት ግብዣ በማድረግ አስተናግደዋል።