የSBS አማርኛ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ ካሣሁን ሰቦቃ የ29ኛው ኩዊል የጋዜጠኛነት ልህቀት ተሸላሚ ሆነ

የSBS አማርኛ ፕሮግራም መጣጥፍ ለአሸናፊነት የበቃው ከግዙፎቹ የአውስትራሊያ ሚዲያ ተቋማት ABC News፣ Herald Sun እና Guardian Australia ጋር ተወዳድሮ ነው።

Quill Awards 2024.jpg

Winner: The 29th Quill Awards for Excellence in Victorian Journalism in Multicultural Affairs and Media, Kassahun Seboqa Negewo, Executive Producer of the SBS Amharic Program (R). Credit: MPC

30 የሽልማት ዘርፎችን ያቀፈው ሥነ ሥርዓት የተካሔድው ዓርብ መጋቢት 6 / 2016 / ማርች 15, 2024 በክራውን ፖላዲየም ነው።

የSBS አማርኛ ፕሮግራም ጋዜጠኛ ካሣሁን ሰቦቃ ነገዎና ጋዜጠኛ ሩቺካ ታልዋር ለሜልበርን ፕሬስ ክለብ በመድብለባሕል ጉዳዮችና ሚዲያ ዘርፍ በአውስትራሊያ ፕሮፌሽናል ጋዜጠኝነት ሙያ የላቀ ደረጃ ያለውን 29ኛውን የኩዊል የጋዜጠኛንት ልህቀት ሽልማት አሸናፊ ለመሆን የበቁት በሚል ርዕስ የኢትዮጵያዊቷን ቤተልሔም ጥበቡ የናሩ ዕገታ ማዕከል ስቃይና የመንፈስ ፅናት አስመልክተው ባቀረቡት መጣጥፍ ነው።

የSBS አማርኛ ፕሮግራም መጣጥፍ ከABC News፣ Herald Sun እና Guardian Australia ጋር ተወዳድሮ ለአሸናፊነት ብቁ የሆነበት ምክንያት "አስደናቂው መጣጥፍ የአውስትራሊያን ቀጪ የኢሚግሬሽን ማዕከል ፖሊሲዎች መርምሯል። ርዕሰ ጉዳዮ ብርቱ ነው፤ እንዲያም ሆኖ ግና ጋዜጠኞች ካሣሁን ነገዎ እና ሩቺካ ታዋር ጥርት ባለ ትረካቸው በጣሙን ሰብዓዊ የሆነ ታሪክ አቅርበዋል።
Kassa Quill.jpg
Kassahun Seboqa Negewo, Executive Producer of the SBS Amharic Program (L), CEO of Gandel Foundation (C), and Shirley Glaister (representative of Journalist Ruchika Talwar - R). Credit: MPC
"በተለይም፤ በጀልባ የመጣችው የታሪኩ ማዕከል ጥገኝነት ጠያቂ ከቶውንም በጣሙን ግላዊ በሆነው ትርክት ተስፋ ቢስ ተደርጋ አልቀረበችም። አንባቢ ከናሩ ዕገታ ማዕከል ተነስቶ በመሸጋገሪያ ቪዛ እስከ አዲስ የሜትሮ ባቡር ቲኬት ተቆጣጣሪነት ሕይወት አዋኪ በሆነው ዘርፈ ብዙ ታሪክ ተስቦ ይገባል" የሚል የዳኞች አስተያየትን በማግኘት ነው።

በዕለቱ በ30 የተለያዩ የጋዜጠኝነት ሙያ ዘርፍ አሸናፊ የሆኑ የአውስትራሊያ ዋነኛ ፕሮፌሽናል ሚዲያ ዝነኛ ጋዜጠኞች ከወርቅ ኩዊል እስከ የሕይወት ዘመን ሽልማቶችን ተቀብለዋል።
Award-winning journalists.jpg
Winners of the Melbourne Press Club’s 29th Quill Awards for Excellence in Victorian Journalism. Credit: MPC

Share

Published

Updated

Source: SBS

Share this with family and friends