" ጾም ስጋን አድክሞ መንፈስን የሚያበረታ መንፈሳዊ ተግባር ነው ። " - መጋቢ አእላፍ ቀሲስ በቃሉ ዳዊት

Kesis Bekalu Dawit

መጋቢ አእላፍ ቀሲስ በቃሉ ዳዊት ጾም በሜልበርን ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እመነት ተካታዮች እየጾሙት ያለውን የአብይ ጾም ሀይማኖታዊ ጠቀሜታውን አስመልከተው ማብራሪያ ሰጥተዋል ።


አንኳሮች
  • አብይ ጾም ፤ ሁዳዴ ፤ ጾመ ኢየሱስ
  • ጾም ለሁሉም አማኒ ግዴታ ነውን ?
  • በጾም ወቅት ከአማኒያኑ ምን ይጠበቃል ?
መጋቢ አእላፍ ቀሲስ በቃሉ ዳዊት ወደ ሀይማኖታዊው አለም ለመጓዝ ፈር የቀደዱላቸው የድጓ መምህር የነበሩት አባታቸው መላከ ሰላም ጥኡመ ልሳን ይልማ እንደሆኑ ይናገራሉ ።

Kesis Bekalu Dawit
በዝዋይ ገዳም ክህነትን ፤ ቅዳሴን እና ሳታትን ከተማሩ በኋላም ወደ ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በመሄድ የዲግሪ ፕሮግራምን መከታተላቸውን ነግረውናል። ወደ አውስትራሊያ ከመምጣታቸውም በፊትም በአዲስ አበባ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሀላፊ በመሆን ለ17 አመታት አገልግለዋል ።
Kesis Bekalu Dawit
መጋቢ አእላፍ ቀሲስ በቃሉ ዳዊት ላለፉት አምስት አመታት እና አሁንም በሜልበርን ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

DSC_0151.JPG

Share