“ ምንም እንኳን ምርመራው መደረጉን ባንቃወምም መንግስት የሄደበት መንገድ ግን ሙሉ መብታችንን ያልጠበቀ ነው፡፡ ” ሲሳይ ታደሰ እና ሜሮን አብርሃ

.

LR-Sisay Kebede Source: Supplied

ከአምስት ቀን በኋላ አንጻራዊ ነጻነታቸውን እያጣጣሙ ካሉትና ፍላሚንግትን በሚገኘው የጋራ መኖሪ ቤቶች ከምኖሩት ሲሳይ ታደሰ እና ሜሮን አብርሃ ጋር ቆይታ አድርገናል ፡፡


በሜልበንርን በጋራ መኖሪ ቤቶች በሚኖሩ ዜጎች ላይ ለአምስት ቀናት ተደርጎ የነበረው እገዳ በዛሬው እለት ተጠናቋል ፡፡

የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ሲባል በቪክቶሪያ መንግስት የተወሰደው ፈጣን እና ነዋሪዎችን ያላስጠነቀቀ እርምጃ ከመነሻው ጀምሮ በርካቶችን  ያስቆጣ ነበር፡፡

“ ምንም እንኳን ምርመራው መደረጉን ባንቃወምም መንግስት የሄደበት መንገድ ግን ሙሉ መብታችንን ያልጠበቀ ነው፡፡ ”  ሲሉ ሲሳይ ታደሰ እና ሜሮን አብርሃ ተናግረዋል ፡፡


Share