ቤተሰብ ምስረታ
አቶ ታክሎ የሱዳንን ድንበር ተሻግረው ለስደተኝነት የተዳረጉት ድርጅታቸው ኢሕአፓ የደርግ አገዛዝ ዒላማ በመሆኑ ልባቸው ተገዢ የነበረው ለኢሕአፓ ፍቅር እንጂ ለተቃራኒ ፆታ አልነበረም።
ታላቁ መፅሐፍ "ለሁሉም ጊዜ አለው" እንዲል፤ፍቅራቸውን ለዛሬዋ ባለቤታቸው ወ/ሮ ገበያነሽ አጋሩ።
ቀለበት ተሳሰሩ።

Engagement ceremony in Sudan. Credit: T.Teshome
ስሟን "አበባ" ሲሉ ሰየሙ።
ጉዞ ወደ አውስትራሊያ
አውስትራሊያ አቶ ታክሎን፣ ባለቤታቸውን ወ/ሮ ገበያነሽንና ልጃቸውን አበባን ተቀበለች።
አዲሱ መኖሪያቸውም በጣት የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ይኖሩባት የነበረችው ሆባርት - ታዝማኒያ ሆነ።

Taklo's family and members of the Tasmania Refugee support group. Credit: T.Teshome
በዓመታት ቆይታቸው ቤተሰባቸው በልጆች በረከት ተመላ። ቁጥሩም በረከተ።

Taklo Teshome and his family. Credit: T.Teshome
'የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት ማኅበራዊ አኗኗርና አገራዊ ተሳትፎ ጥንካሬው የላላ ነው' የሚል አተያይም አላቸው።