"በኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ዘንድ ያለው መናናቅ፣እኔ ብቻ ነኝ ዐዋቂ የሚለውና የዘር ፖለቲካ ክፍፍል ቅር ያሰኘኛል" ደራሲ ታክሎ ተሾመ

Taklo Teshome Pic 2.jpg

Taklo Teshome. Credit: SBS Amharic

የስደት ሕይወት ፈታኝነት የአደባባይ ምስጢር ነው። ለስኬት ለበቁት እንኳ እሾሃህን የተላበሰ ጽጌረዳ ነው። ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ በአገረ ሱዳን የስደት ሕይወታቸው አገር ቤት ትተውት የወጡት ልጃቸው ናፍቆት ተጨምሮ፤ ሌሎች በርካታ ፈተናዎች ተቀንሰው፤ በማሽላ ቆረጣና ውኃ ሽያጭ ለመተዳደር ግድ ተሰኝተዋል። ዘግየት ብለው የአንድ መኪና መለዋወጫ ሱቅ ሥራ አስኪያጅ ለመሆን እስከበቁ ድረስ።


ቤተሰብ ምስረታ

አቶ ታክሎ የሱዳንን ድንበር ተሻግረው ለስደተኝነት የተዳረጉት ድርጅታቸው ኢሕአፓ የደርግ አገዛዝ ዒላማ በመሆኑ ልባቸው ተገዢ የነበረው ለኢሕአፓ ፍቅር እንጂ ለተቃራኒ ፆታ አልነበረም።

ታላቁ መፅሐፍ "ለሁሉም ጊዜ አለው" እንዲል፤ፍቅራቸውን ለዛሬዋ ባለቤታቸው ወ/ሮ ገበያነሽ አጋሩ።

ቀለበት ተሳሰሩ።
Engagement.jpg
Engagement ceremony in Sudan. Credit: T.Teshome
አዲሶቹ ባለ ቀለበቶች ወራት አስቆጥረው የመጀመሪያ ልጃቸውን አፈሩ።

ስሟን "አበባ" ሲሉ ሰየሙ።

ጉዞ ወደ አውስትራሊያ

አውስትራሊያ አቶ ታክሎን፣ ባለቤታቸውን ወ/ሮ ገበያነሽንና ልጃቸውን አበባን ተቀበለች።

አዲሱ መኖሪያቸውም በጣት የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ይኖሩባት የነበረችው ሆባርት - ታዝማኒያ ሆነ።
2022-12-09_16-49-10.png
Taklo's family and members of the Tasmania Refugee support group. Credit: T.Teshome
እምብዛም ሳይቆዩ ግና እስካሁንም ወደ አሉባትና በርካታ ኢዮጵያውያን ወደ ሚኖሩባት ሜልበርን ከተማ ጓዛቸውን ሸክፈው ከቤተሰባቸው ጋር ከተሙ።

በዓመታት ቆይታቸው ቤተሰባቸው በልጆች በረከት ተመላ። ቁጥሩም በረከተ።
Family.jpg
Taklo Teshome and his family. Credit: T.Teshome
ደራሲ ታክሎ ተሾመ፤ በግል ኑሯቸው ደስተኛ እንደሆኑ ይገልጣሉ።

'የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት ማኅበራዊ አኗኗርና አገራዊ ተሳትፎ ጥንካሬው የላላ ነው' የሚል አተያይም አላቸው።

Share