ኮሮናቫይረስን ለመገደብ የተጣሉ አዳዲስ ገደቦች ሥራ ላይ መዋል ጀመሩ

A person orders takeaway at a cafe which has closed its indoor seating area Source: AAP
ዛሬ ማርች 23 ከቀትር በኋላ ጀምሮ የኮሮኖቫይረስ መዛመትን ለመገደብ የተጣሉትን አዳዲስ ገደቦች ሥራ ላይ መዋል ጀምረዋል። የተወሰኑ ግልጋሎቶቻቸው ግድ የማያሰኙ የንግድ ተቋማት ሲዘጉ፤ የገበያ አዳራሾችና ባንኮችን የመሳሰሉ ግልጋሎት ሰጪዎች ለሕዝብ ክፍት ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ። ቪክቶሪያ እገዳ የተጣለባቸው ግድ የማያሰኙ ግልጋሎቶችና እራሳቸውን እንዲያገሉ የተባሉ ግለሰቦች ውሳኔዎቹን በተግባር ማዋል - አለማዋላቸውን የሚቆጣጠሩ 500 ልዩ የፖሊስ ኃይል አሰማርታለች።
Share