ንፅፅሮሽ - ኢትዮጵያና አውስትራሊያ፤ "ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ አየሁ" የመጀመሪያ ጊዜ መራጭ ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ

Journalist Elias Gudisa. Credit: E.Gudisa
ጋዜጠኛ ኤልያስ ጉዲሳ፤ ሀገር ቤት የጋዜጣና መፅሔት አሳታሚና ባለቤት ሆኖ ዘግቧል። በድምፅ ሰጪነትም ተሳትፏል። በኬንያ የስደት ሕይወቱም ድኅረ ምርጫ ያስከተላቸውን የሕይወት ጥፋትና የንብረት ውድመት ትኩረት ሰጥቶ ተመልክቷል። በሀገረ አውስትራሊያም ፍልሰተኛ ሆኖ የምርጫ ክንውኖች በቅርበት ተከታትሏል። የአውስትራሊያን ዜግነት ከተላበሰ ወዲህ ግና በሀገር አቀፍ ምርጫ የአውስትራያን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ለመቅረፅና ለመገንባት በድምፅ ሰጪነት ቀጥተኛ የዜግነት ድርሻውን ሲወጣ የዘንድሮው የ2025 ፌዴራል ምርጫ የመጀመሪያው ነው። ምልሰታዊ ምልከታውን ከአሁናዊ ተሞክሮው ጋር አሰናስሎ ንፅፅሮሹን ያጋራል።
Share